@ebcnewsnow · Post #54033 · 25.04.2026 г., 17:18
ከጥገኝነት ራስን ወደ መቻል፦ የአሊኮ ዳንጎቴ የ650 ሺህ በርሜል የማጣሪያ ፕሮጀክት ውጥን ለምስራቅ አፍሪካ ********************* የዳንጎቴ ግሩፕ ፕሬዚዳንት አሊኮ ዳንጎቴ፣ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መንግሥታት አስፈላጊውን ድጋፍ ካደረጉላቸው በቀን 650 ሺህ በርሜል ድፍድፍ ዘይት የማጣራት አቅም ያለውን የሪፋይነሪ ሞዴላቸውን በቀጣናው ለመድገም ቃል ገብተዋል። በናይሮቢ በተካሄደው የ‘አፍሪካ ዊ ቢልድ ሰሚት 2026’ ላይ ንግግር ያደረጉት ዳንጎቴ፣ አፍሪካ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ራሷን መቻል ላይ ትኩረት እንድታደርግ እና ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ያላትን ጥገኝነት እንድትቀንስም ጥሪ አቅርበዋል። ዳንጎቴ በንግግራቸው፣ በናይጄሪያ በማስፋፊያ ግንባታ ሂደት ላይ የሚገኘው እና በቀን 650 ሺህ በርሜል የሚያጣራው የሪፋይነሪ ፕሮጀክት ለተመሳሳይ የምስራቅ አፍሪካ ኢንቨስትመንት እንደ መነሻ (blueprint) ሆኖ እንደሚያገለግል ገልጸዋል። “ቃል የምገባው ነገር ቢኖር፣ የቀጣናው ሀገራት ድጋፍ ካደረጉልን በናይጄሪያ ያለውን ዓይነት በቀን 650 ሺህ በርሜል ድፍድፍ ዘይት የሚያጣራ ፋብሪካ በምስራቅ አፍሪካ እንገነባለን፣ ውጤታማም እንሆናለን፤ ይህን በናይጄሪያ በተግባር ሠርተን አሳይተናል” ብለዋል ዳንጎቴ። ይህን ግዙፍ ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ግን የቀጣናው መንግሥታት ቁርጠኝነት እና የመሠረተ ልማት ዝግጁነት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። በሔዋን ጌታቸው #DngoteGroup#AlikoDangote#EastAfrica#Refinery#650000bpd#EBC