TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← Borkena
Borkena avatar

TGINSIGHT POST

Post #6035

@borkena

Borkena

Views1,140Post view count
PostedMar 1603/16/2026, 12:10 PM
Post content

Post content

ቭላድሚር ፑቲን በጋሞ በደረሰው ክስተት ሀዘናቸውን ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ ተወያይተዋል። ውይይቱ በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር የፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት ቃል አቀባይ ዲሜትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። ፑቲን በጋሞ ዞን የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል ተብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በበኩላቸው በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ "ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ የስልክ ውይይት አድርገናል" ሲሉ አጭር አስተያየት አስፍረዋል። #Ethiopia#ethiopiannews#Ethiopia_Russia#news#putin#PMAbiyAhmed#VladimirPutin#news#ዜና#ኢትዮጵያ#ሩሲያ#ጋሞ#ቦርከና_ዜና