TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← Nor Radio
Nor Radio avatar

TGINSIGHT POST

Post #274

@NorRadio1

Nor Radio

ዕይታዎች900የዕይታ ቁጥር
ታትሟልኤፕሪ 2727/04/2026 08:33 ጥዋት
ይዘት

የልጥፍ ይዘት

🔶በፌስቡክ ከፍተኛ ተከታይ ያላቸው የአፍሪካ መሪዎች በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ መሪዎች ከመደበኛው የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን በበለጠ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም ከዜጎቻቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት እያጠናከሩ ይገኛሉ። በቅርቡ የወጣ መረጃ እንደሚያሳየው፣ መሪዎቹ የሥራ አፈጻጸማቸውንና አገራዊ መረጃዎችን ለሕዝብ ለማድረስ ፌስቡክን ዋነኛ መድረክ አድርገውታል። በአህጉሪቱ በፌስቡክ ገጻቸው ከፍተኛ ተከታይ በማፍራት የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ ኤል-ሲሲ በ12 ሚሊዮን ተከታዮች ቀዳሚነቱን ይዘዋል። የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በበኩላቸው በ6.8 ሚሊዮን ተከታዮች በአህጉሪቱ ከፍተኛ ተጽዕኖ ካላቸው መሪዎች መካከል በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ። በምሥራቅ አፍሪካ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በ3.9 ሚሊዮን ተከታዮች የዲጂታል ተደራሽነታቸውን እያሰፉ ሲሆን፣ በደቡባዊ አፍሪካ ደግሞ የዛምቢያው ፕሬዝዳንት ሀካይንዴ ሂቺሌማ በ2.2 ሚሊዮን ተከታዮች ተጠቃሽ ናቸው። የጋናው ጆን ድራማኒ ማሃማ (1.8 ሚሊዮን) እና የሩዋንዳው ፖል ካጋሜ (1.7 ሚሊዮን) ተከታዮችን በማፍራት ቀጣዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል። በምዕራብ አፍሪካ የሴኔጋሉ ኡስማን ሶንኮ በ1.4 ሚሊዮን ተከታዮች ከፍተኛ እድገት እያሳዩ ሲሆን፣ የቦትስዋናው ዱማ ጊዴዎን ቦኮ እና የኮትዲቯሩ አላሳን ዋታራ እያንዳንዳቸው 1.3 ሚሊዮን ተከታዮች አሏቸው። የናይጄሪያው ፕሬዝዳንት ቦላ አህመድ ቲኑቡ በበኩላቸው በ1.1 ሚሊዮን ተከታዮች በአህጉሪቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ መሪዎች ተርታ ተመድበዋል። ==================== አሁኑኑ የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇 https://t.me/NorRadio1 https://t.me/NorRadio1