TGTGInsightтелеграм анализLIVE / telegram public index
← Такты, стеки, два колеса

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Намери подобно съдържание

Изходен канал @clockstackwheels · Post #1237 · 7.05

В 2023 году мы с коллегой сделали доклад на DotNext по DDD и архитектуре систем. И там, в числе прочего, показали, что устройство сложного проекта, спроектированного по определённым правилам, может иметь фрактальную структуру. Но мысль эту особо не развивали. В 2024 году Влад Хононов — автор одной из самых известных книг по DDD — сделал доклад на DotNext по теме «Фрактальная геометрия в проектировании систем». Разумеется, он никаким образом на нашу идею не опирался, а работал над своей системой уже несколько лет к моменту доклада. У него там прям интересные научные обоснования, более серьёзный теоретический фундамент с введением новых понятий и принципов. Но факт близости хода мысли приятен. Типа, мы с коллегой делали систему, которая показала те же свойства, что и системы крутого эксперта в архитектуре. Прям рекомендую доклад по второй ссылке всем, кто работает в компаниях, где по какому-то странному недосмотру есть архитектура, борьба с техдолгом и попытки не допустить превращения кода в лапшу с высоким зацеплением. #dev@clockstackwheels

Hashtags

Резултати

Намерени 7 подобни публикации

Търсене: #ausummit2026

当前筛选 #ausummit2026清除筛选

ኢትዮጵያ እንግዶቿን በክብር እየሸኘች ነው **************** በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤና በ2ኛው የጣሊያን-አፍሪካ ስብሰባ ላይ የተሳተፉ መሪዎች በኢትዮጵያ የነበራቸውን ቆይታ በስኬት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ወደ አገራቸው መመለስ ጀምረዋል። መሪዎቹ ከቦሌ ዓለም-አቀፍ አየር ማረፊያ ሲነሱም የክብር አሸኛኘት እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#ebcdotstream#Ethiopia#AUSummit2026

ለ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ከእንግዶች አቀባበል ጋር በተያያዘ ዝግ የሚደረጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ ******************** የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል 39ኛውን የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ አስመልክቶ አጠቃላይ የጸጥታ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወቅ ሲሆን የተሽከርካሪ ፍሰቱን ለማሳለጥና ከእንግዶች አቀባበል ጋር በተያያዘ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። በዚህም ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ብራስ እንዲሁም ከቦሌ መድኃኒያለም በአትላስ ወደ ቅዱስ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ በመሪዎቹ ጉባኤ ምክንያት ከዛሬ የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረግ ይሆናል። በተጨማሪም በሌሎች እንግዶች በሚያርፉባቸው ዋና ዋና አደባባዮችና የአጀብ መስመሮች አሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠትና የትራፊክ ፖሊስ አባላትን ትዕዛዝ በማክበር የተለመደ ቀና ትብብራቸውን እንዲያደርጉ፤ በተጠቀሱት ቦታዎች ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪዎችን ማቆም የተከለከለ መሆኑንም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙም በነጻ የስልክ መስመሮች 990፣ 991፣ 987፣ 816 እንዲሁም በ011-1-26-43-59፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (Citizen Engagement Application) EFPApp በመጠቀም ጥቆማ መስጠት እንደሚገባም ጥሪ ተላልፏል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#AUSummit2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ጋር ተወያዩ ******* አዲሱን የኅብረታችን ሊቀመንበር፤ የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬን አግኝቼ በተረከቡት ኃላፊነት ደስታዬን ገልጬላቸዋለሁ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የአፍሪካውያን ጠንካራ ትብብር እና ቀጣናዊ ግንኙነቶችን ለማሳደግ በሚያስችሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገናል ብለዋል። #EBC#PMAbiy#Ethiopia#AUSummit2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቦትስዋና ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮን ጋር ተወያዩ ****************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቦትስዋና ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ የቦትስዋና ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮን አግኝቼ፤ በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች፣ ለተሻለ ኢኮኖሚያዊ ትብብር ያሉ እድሎች እና አፍሪካን ቀጣይ የሚመራ ትውልድን ማብቃት ላይ በጋራ በምንሰራበት አውድ ዙሪያ ውይይት አድርገናል ብለዋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#PMAbiy#Diplomacy#AUSummit2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ፕሬዝዳንታዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር መሃመድ አልመንፊ ጋር ተወያዩ ***************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ፕሬዝዳንታዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር መሃመድ አልመንፊ ጋር በቀጣናዊ ልማት እና የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#PMAbiy#Diplomacy#AUSummit2026

የተመድ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አዲስ አበባ ገቡ **************** የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በ39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል። ዋና ጸሀፊው ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የፕላንና ልማት ሚኒስተር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል። 39ኛው የኅብረቱ የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፥ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ ይካሄዳል። በጉባኤው የሚሳተፉ መሪዎችም ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ በመግባት ላይ ናቸው። በሞላ አለማየሁ #EthiopianBroadcastingCorporation#Ethiopia#UNSG#AntónioGuterres#AUSummit2026

ከጉባኤ አዳራሾች ባሻገር የሚተርክ አዲስ ገጽታ እና የኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊ ዝግጁነት ******************* ኢትዮጵያ 39ኛውን የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 2ኛውን የጣሊያን-አፍሪካ ስብሰባ ለመካፈል ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ከፍተኛ ልዑካንን ለመቀበል ከመቼውም ጊዜ በላይ ስንዱ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። መዲናዋ በከፍተኛ ጥራትና በዘመናዊ መልክ የተገነቡ ዓለም አቀፍ የስብሰባ አዳራሾችን እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ ምቹ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማሟላት እንግዶቿን ለመቀበል በላቀ ደረጃ መዘጋጀቷን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። ይህ አዲሱና ማራኪው የከተማዋ ገጽታ የእንግዶችን ቆይታ ልዩና የማይረሳ እንደሚያደርገው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተሳታፊዎች ከጉባኤው መድረኮች ባሻገር በአፍሪካውያን ጥረት እያደገ የመጣውን አዲሱን የቱሪዝም ዘርፍ እንዲመለከቱና ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ይህ ዝግጁነት ኢትዮጵያ ለዲፕሎማሲያዊ ሁነቶች ያላትን ምቹነት የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን፣ አህጉራዊ ትብብርንና የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ያረጋገጠ መሆኑ ተመላክቷል። #Ethiopia#PMAbiyAhmed#AfricanUnion#AUSummit2026#ItalyAfricaSummit#TourismEthiopia#EthiopianBroadcastingCorporation