@ethiofunnyjokess · Post #28201 · 12.04.2026 г., 06:02
🕊️ ከአንድ እንጀራ በላይ... ልብን ማካፈል! በዚህች አለም ላይ "ምንም የለኝም" የሚል ደሃ የለም፤ ምክንያቱም ሁሉም ሰው የሚሰጠው አንድ ነገር አለው—ፍቅር! ዛሬ ማዕድህ ላይ የፈለገው አይነት ጣፋጭ ምግብ ቢኖር፣ ብቻህን ከበላኸው ጣዕሙ ሆድህ ጋ ያበቃል። ለተራበ ወንድምህ ወይም በጎዳና ላለች እህትህ ስታካፍል ግን ጣዕሙ ሰማይ ይደርሳል። መስጠት ከኪስ የሚወጣ ብር ሳይሆን፣ ከልብ የሚመነጭ መድኃኒት ነው። ለነዳያን ስንሰጥ የምናደርገው ውለታ ሳይሆን፣ የሰውነታችንን ግዴታ እየተወጣን መሆኑን አንርሳ። * አንተ ጋ የተረፈው ፍርፋሪ፣ ሌላው ጋ የሳምንት ህልም ሊሆን ይችላል። አንተ ጋ "ቅያሪ የለኝም" ብለህ የምታልፋት ሳንቲም፣ ሌላው ጋ የዕለት ጉርስ ልትሆን ትችላለች። እውነተኛ በዓል ማለት አዲስ ልብስ መልበስ ሳይሆን፣ የቆሰለ ልብን በፍቅር ጠግኖ አብሮ መብላት ነው። ሺዎች መሆን ማለት ሺዎች የሚራራ ልብ ማለት ነው። ዛሬ አንድ ሰው ደስ እንዲለው ምክንያት እንሁን። ያለንን ስናካፍል፣ የጎደለን ይሞላል! መልካም የትንሳኤ በዓል! ❤️✨ #Share❤
Hashtags