TGTGInsightтелеграм анализLIVE / telegram public index
← Такты, стеки, два колеса

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Намери подобно съдържание

Изходен канал @clockstackwheels · Post #310 · 21.04

Поймал себя на том, что иногда мне нравится ездить на автомобиле, а иногда нет. Понятно, что чилить на автостраде это прикольно, а пробиваться через городские пробки — нет. Но я осознал, что иногда мне в городе вполне прикольно, а иногда нет. Я даже в пробках иногда стою спокойно. Начал рефлексировать, и понял: мне приятно ездить, когда я никуда не тороплюсь. Когда можно опоздать на 5-10-15 минут, а то и на полчаса. В гости к друзьям обычно можно опоздать. В магазин можно опоздать, если ты не под закрытие едешь. А вот если едешь на какое-то мероприятие ко времени, то опаздывать нельзя, и обычно даже 10 минут неприятны. Дорожная ситуация меняется не слишком предсказуемо. Время на поиск места парковки тоже не определено. Да и постоянное искушение где-то что-то нарушить, чтобы не опоздать. Либо наоборот — выезжаешь на машине сильно заранее, и на месте просто ждёшь полчаса. В общем, машина хорошо решает задачу "Добраться куда-то в место, плохо доступное другими видами транспорта". Но не слишком хорошо решает задачу "Добраться куда-то к заданному моменту с точностью плюс-минус 5 минут". А, например, пешком + метро решает хорошо. Можно, конечно, пофантазировать на тему какого-то предсказания и правильного планирования, но на деле пара забитых перекрёстков вполне могут стоить вам 10 минут, что в контексте городской жизни довольно много. P.S. Скоро у меня отпуск, и будут очень интересные посты про дроны и мототехнику. Хотя погода в Питере как обычно норовит подвести в самое неподходящее время. С таким климатом хоть на автомобиле езди! #life

Hashtags

Резултати

Намерени 76 подобни публикации

Търсене: #pmoethiopia

当前筛选 #pmoethiopia清除筛选

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በአንድነት ፓርክ ዓመታዊውን የፋሲካ መዐድ ማጋራት አከናወኑ ************** በመላው ኢትዮጵያ በክርስትና ጥላ ውስጥ በሚገኙ ቤተ-እምነቶች ያሉ ክርስቲያኖች የትንሳኤን በዓል በተስፋ፣ በመስዋዕትነት እና በአዲስ መነሳት መንፈስ በአንድነት ያከብራሉ። ከሳምንታት የፆም፣ ጥሞና እና ራስን የመመልከት ጊዜ በኋላ ፋሲካ በእውነተኛ አምልኮ፣ መንፈስን አድሶ፣ ቤቶችንም በደስታ ይሞላል። በዘመድ አዝማድ መጠያየቅ እና ማዕድ መካፈልም ፍቅርን ያዳብራል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ዓመታዊውን የፋሲካ መዐድ ማጋራት ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር በአንድነት ፓርክ በጋራ መታደማቸው ለእውነተኛው የአንድነት መንፈስ ጉልህ ማሳያ ነው። በዓለ ትንሳኤው በመላው ኢትዮጵያ የእምነት፣ ቤተሰባዊነት እና የመታደስ መንፈስ የሚታይበት ጊዜ ነው። ሁላችንም በዚህ የትንሳኤ መንፈስ ዛሬም፣ ነገም፣ ሰርክ ቤታችንን፣ ልባችንንም ለተቸገሩ ወገኖች እንክፈት! መልካም በዓል። #PMOEthiopia

Hashtags

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ገመገሙ ******************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርትን ገምግመዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ አመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦላቸው በውጤቶቹ ላይ ግምገማ እና ውይይት መደረጉንም የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አስታውቋል። #PMOEthiopia

Hashtags

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ ***************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች ሹመት ሰጥተዋል። በዚሁ መሠረት፦ - ሌ/ጄኔራል አስራት ደኔሮ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር - ረዳት ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር - አቶ ኤርዚቅ ኢሳ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል #PMOEthiopia

Hashtags

Ethiopian News Agency

@ethiopiannewsa · Post #27428 · 28.04.2026 г., 14:12

የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በጤና ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶችን ባቀረቡት ሪፖርት፦ ዘርፉ ከለውጡ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን በመለየት ካስመዘገባቸው ዋና ዋና ስኬቶች መካከል፤ ለ30 ዓመታት የቆየው የጤና ፓሊሲን በመከለስ፣ መከላከል ከሚለው መርህ በተጨማሪ አክሞ የማዳን ቁርጠኛ የፖሊሲ አመራር፣ የተቋም ግንባታ፣ የጤና መሠረተ ልማት ለውጦች፣ መድሃኒት፣ ክትባት እና የህክምና ግብዓቶች ምርት አቅርቦት እና ቁጥጥር ጭማሪ እንዲሁም የጤና ፋይናንስ እመርታ ቁልፍ እና ዋነኞቹ የለውጥ ስራዎች ናቸው። ‎በተለይም የወረርሽኝ ልየታ እና ቁጥጥር፣ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና እንክብካቤ፣ የጤና ባለሙያዎችን ማብቃትና ቁጥራቸውን ማሳደግ፤ የዲጂታል ጤና፣ በዘርፉ የተተገበሩ ልዩ ልዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ኢትዮጵያ በጤና ዘርፍ ያስመዘገበቻቸው ግንባር ቀደም ስኬቶቿ ናቸው። ‎ የጤና ዲፕሎማሲ ዘርፍ ከፍ ያሉ እመርታዎች የተመዘገበበት አንዱና ዋነኛው መስክ ሲሆን ኢትዮጵያ በተለያዩ መድረኮች ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመርጣ ድርድሮችን እና ንግግሮችን እንድትመራ አስችሏታል። #PMOEthiopia

Hashtags

Ethiopian News Agency

@ethiopiannewsa · Post #27427 · 28.04.2026 г., 13:58

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በትምህርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶችን አቅርበዋል። ‎ ከለውጡ በፊት የትምህርቱ ዘርፍ በእጅጉ የተጎዳ፣ ሰፊ እና አፋጣኝ ተሀድሶ ከሚያስፈልጋቸው ዘርፎች አንዱ ነበር። ዘርፉን በእጅጉ ተጭነውት ከነበሩ ችግሮች መካከል፤ የመሠረተ ልማት ጥራትና የግብዓት እጥረት፣ የተማሪ-መምህር፣ የተማሪ-ክፍል ጥመርታ አለመመጣጠን፣ ለትምህርት ዓይነቶች ብቁ የሆኑ መምህራን አለመኖር፣ የስርዓተ ትምህርት አግባብነትና የመጻህፍት ተደራሽነት ችግሮች፣ ኢ-ፍትሃዊነትና ኢ-እኩልነት፣ የትምህርት ሴክተሩ ትክክለኛነት መዳከም፣ ዝቅተኛ የቅድመ መደበኛ ትምህርት መኖር ከብዙ ማነቆዎች ጥቂቶች ነበሩ። ‎ በዚህም በጥናት በተደገፈ መልኩ፤ የትምህርት ዘርፉን ፍላጎቶች እና ተግዳሮቶች በመለየት ከተመዘገቡ ዋና ዋና ለውጦች መካከል፤ የሥርዓተ-ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ፣ የመፅሃፍት ህትመት ስርጭትና ተደራሽነት፣ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት፣ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ማሳደግ፣ የትምህርት ቤት ደረጃ ማሻሻል፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሪፎርም፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን እና ዲጂታል ትምህርት መስፋፋት፣ የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ዝግጅትና አስተዳደር መሻሻል፣ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማደግ ዋነኞቹ በለውጡ ተግባራዊ የሆኑና ውጤት ያስገኙ ሆነው ተመዝግበዋል። #PMOEthiopia

Hashtags

Ethiopian News Agency

@ethiopiannewsa · Post #27421 · 28.04.2026 г., 11:36

አሁን በመካሄድ ላይ! ‎ ‎‘’የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ’’ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው እና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ፤ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት መካሄድ ጀምሯል። ‎ባለፉት ስምንት አመታት በተለይም በትምህርት፣ ጤና፣ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በባህል፤ በኪነ-ጥበብና ስፖርት እንዲሁም በሴቶች እና ማሕበራዊ ጉዳዮች የተመዘገቡ ውጤቶች በስፋት የሚተነተኑበት መድረክ ነው። #PMOEthiopia

Hashtags

Ethiopian News Agency

@ethiopiannewsa · Post #27407 · 27.04.2026 г., 17:27

የጋራ መተማመን እና ዕድገት በሰነቀ ርዕይ ላይ የተመሠረተው የኢትዮጵያ እና ሞዛምቢክ ግንኙነት ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ተሸጋግረዋል። ‎ ‎ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ በተገኙበት፤ በወታደራዊ ሥልጠና፣ በከተማ ልማትና በቤት ግንባታ፣ በጤና፣ በሲቪል አቪዬሽን፣ በቱሪዝም እንዲሁም በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፤ በተለይም በዲጂታል መታወቂያ እና ዲጂታል የሕዝብ መሠረተ ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ታሪካዊ የመግባቢያ ሰነዶች ተፈርመዋል። ‎እነዚህ ስምምነቶች ከፖሊሲ ሰነድነት ባለፈ ለጋራ ብልጽግና ተጨባጭ መንገዶችን የሚቀይሱ ናቸው። ‎ ‎የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ሀገራችን የደረሰችበትን ልምድና እውቀት ለአፍሪካውያን ወንድሞቿ ለማካፈል ያላትን ቁርጠኝነት የምታረጋግጥ ሲሆን፤ በእንዲህ ዓይነት አጋርነቶችም በጋራ ለመማር እና ለማደግ ዝግጁ ናት። #PMOEthiopia

Hashtags

Ethiopian News Agency

@ethiopiannewsa · Post #27391 · 27.04.2026 г., 15:19

በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ሙዚየም የተደረገ ጥልቅ የታሪክ ጉዞ! ‎የሞዛምቢክ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖ በኢትዮጵያ እያደረጉት ያለው ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አካል የሆነውን የብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ሙዚየምን ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ የኢትዮጵያን ነፃና ጥንታዊ ሥልጣኔ የሚያሳይ ሲሆን፤ የሀገሪቱ ታሪክና ቅርሶችም ለታማኝና ባለርዕይ አጋርነቷ ህያው ምስክሮች ሆነዋል። ኢትዮጵያ ምድረ ቀደምት መሆኗን የሚያሳዩ ታሪካዊ ቅርሶቿን ስታጋራ፣ ጥንታዊ ጥንካሬዋ ለዘመናዊውና ለውጥን ለሚያረጋግጠው አጋርነቷ መሠረት መሆኑን በድጋሚ እያረጋገጠች፤ አፍሪካውያን ወንድሞቻችንን ለጋራ የወደፊት ዕጣ-ፈንታ በአንድነት ለመሥራት ወደ ሁለተኛ ቤታቸው እንዲመጡ ጥሪ የምታቀርብበት ነው። #PMOEthiopia

Hashtags

Ethiopian News Agency

@ethiopiannewsa · Post #27372 · 27.04.2026 г., 10:50

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሞዛምቢክ ፕሬዝደንት ዳንኤል ፍራንሲስኮ ቻፖን በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በክብር አቀባበል አድርገውላቸዋል። ‎ ‎የፕሬዝደንቱ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የጋራ ልማትና የህዝብ ለህዝብ ትስስር ትርጉም ባለው መልኩ ሊለውጡ የሚችሉ ተጨባጭ ስራዎችን ቅድሚያ የሰጠ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ ለእውነተኛ አፍሪካዊ አጋርነት ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ነው። #PMOEthiopia

Hashtags

Ethiopian News Agency

@ethiopiannewsa · Post #27307 · 24.04.2026 г., 15:36

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ከሰአት በኋላ የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን በብሔራዊ ቤተመንግሥት ተቀብለዋል። የመሪዎቹ ግንኙነት ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር በኢትዮጵያ የሚያደርጉት የሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት አካል ነው። የመሪዎቹ ውይይት በሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና የወል የትብብር መስኮችን በማጠናከር ላይ እንደሚያጠነጥን ይጠበቃል። #PMOEthiopia

Hashtags

Ethiopian News Agency

@ethiopiannewsa · Post #27256 · 22.04.2026 г., 08:37

ዛሬ ስራ የጀመረው የመሶብ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ አገልግሎት፣ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሰራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ስርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ ነው። ‎አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ስርዓት ያለው ሲሆን፣ የተለያዩ የክፍያ አማራጮችንም አካቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል ከ8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝ ሲሆን፤ አስተማማኝ ኢንተርኔትም ተገጥሞለታል። ‎ ‎ በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡን ደህንነትና ግልፅነትን ለመከታተል ካሜራዎች ተገጥመውለታል። መፍትሔ አምጪ ሆኖ የተዘጋጀው የፈጠራ ውጤትና ተንቀሳቃሽ ክፍል፤ ከስምንት የተለያዩ የመንግስት ተቋማት የሚገኙ የሚከተሉትን ወሳኝ አገልግሎቶች ይሰጣል፦ ‎• አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) መስጠት ‎• የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ ‎• ለመንጃ ፈቃድ የሚያስፈልግ የህክምና ምርመራ ማድረግ ‎• የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ ‎• የመንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ ‎• የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያን ማከናወን ‎• የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት ‎• በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሚሰጥ የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን ይሰጣል። ‎ ‎በአጠቃላይ ይህ ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የስምንት ተቋማትን አገልግሎት በአንድ ላይ በማቀናጀት፣ ዜጎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ወይም የተለያዩ ቢሮዎችን ማንኳኳት ሳያስፈልጋቸው ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ መፍትሄ ይሰጣል። #PMOEthiopia

Hashtags

123•••67
ПредишнаСтр. 1 от 7Следваща