TGTGInsightтелеграм анализLIVE / telegram public index
← Такты, стеки, два колеса

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Намери подобно съдържание

Изходен канал @clockstackwheels · Post #339 · 9.05

Наконец попробовал полетать в FPV-режиме вживую, и это невероятное ощущение. Ни с чем не могу сравнить: в симуляторе похожее управление, но совершенно нет эффекта погружения и адреналина из-за риска разбиться. А обычные дроны, как у меня были раньше, даже в FPV-очках не передают чувство контроля и скорости. Короче, очень круто. Не зря потрачены долгие дни на обучение. Пока страшно, и дёргаюсь в полёте как невротик, но уже супер кайфово. У меня не будет для вас пафосного FPV-ролика из тех, что вы видели на ютубе. Не с первого раза точно, да и место хорошее нужно долго выбирать. Но за этот год я планирую всё-таки несколько таких роликов сделать. #drone#hobby

Hashtags

Резултати

Намерени 4 подобни публикации

Търсене: #gamozone

当前筛选 #gamozone清除筛选
Borkena

@borkena · Post #6006 · 13.03.2026 г., 18:05

የ3 ቀናት ብሔራዊ ሀዘን ታወጀ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተው የመሬት ናዳ እና የጎርፍ አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች የ3 ቀናት ብሔራዊ ሀዘን ታውጇል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፥ በዞኑ ጋጫ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ከጠፉ 125 ሰዎች ውስጥ የ80 ወገኖችን ሕይወት ማለፉን ገልፀዋል። የቀሪ ሰዎች አስከሬን ፍለጋ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ምክር ቤቱ በዜጎቻችን ላይ በተከሰተው አደጋ ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶታል ብለዋል። በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፕብሊክ የሰንደቅ አላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001 አንቀጽ 22 ንዑስ አንቀጽ (2) ብሔራዊ የሀዘን ቀንና ሰንደቅ አላማው ዝቅ ብሎ የሚውለበለብባቸውን ሁኔታዎች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ መደንገጉን ተናግረዋል። በዚሁ መሠረት በመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወታቸው ያለፈው ዜጎቻችንን በማስመልከት ከመጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ቀናት ብሔራዊ የሀዘን ቀን ታውጇል ብለዋል። በእነዚህ ቀናት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰንደቅ አላማ በሁሉም የሀገሪቱ ግዛቶች፣ በኢትዮጵያ መርከቦች፣ በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንጽላ ጽ/ቤት ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ ውሳኔ መተላለፉን ገልፀዋል። #Ethiopia#News#gamozone#ዜና#የጎርፍአደጋ#ጋሞዞን#ቦርከና_ዜና

Borkena

@borkena · Post #5985 · 12.03.2026 г., 13:56

በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት የሟቾች ቁጥር 107 ደረሰ። ​በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ፣ ካምባ እና ቦንኬ ወረዳዎች በደረሰ የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ የ107 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ​ዋና አስተዳዳሪው በአደጋው 127 ሰዎች መጥፋታቸው እና እስካሁን አለመገኘታቸውን ገልፀዋል። በአካባቢው መልከዓ ምድር አስቸጋሪነት ምክንያት አስክሬን ፍለጋው መጓተቱን ተናግረዋል። ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የዕለት እርዳታ እየቀረበ መሆኑን ጠቁመዋል። ​​#Ethiopia#gamozone#South_Ethiopia#ዜና#ቦርከና_ዜና#ጋሞዞን#የጎርፍአደጋ

Borkena

@borkena · Post #5968 · 10.03.2026 г., 11:48

እናት ከሁለት ልጆቿ ጋር በመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸው አለፈ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቦንኬ ወረዳ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የአንድ ቤተሰብ የሆኑ እናትና ሁለት ልጆች ሕይወታቸውን አጥተዋል። አባወራው ከፍተኛ ጉዳት ተደርሶባቸው በቦንኬ ጋዜሶ ጤና ጣቢያ ህክምና እየተደረገላቸው ነው ተብሏል። ከአርባ ምንጭ–ጊና–ቦንኬ የሚያገናኘው ዋና መንገድ በመሬት መንሸራተት ተዘግቶ በመገኘቱ ተጎጂውን ወደ ሆስፒታል ለማድረስ ችግር መፍጠሩ ተገልጿል። ዞኑ በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳና በከምባ ዙሪያ ወረዳ አካባቢዎች የጎርፍ ስጋት መኖሩን የጋሞ ዞን ፖሊስ አስጠንቅቋል፤ ነዋሪዎችም ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪውን አቅርቧል። ​ #Ethiopia#Borkena_news#Ethiopiannews#gamozone#አርባምንጭ#ጋሞዞን#ዜና#ቦርከና_ዜና