TGTGInsightтелеграм анализLIVE / telegram public index
← Такты, стеки, два колеса

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Намери подобно съдържание

Изходен канал @clockstackwheels · Post #569 · 25.09

Недавно в сеть слили утекшие материалы GTA 6: видео с игровым процессом (сырым и с сырой графикой, конечно). Пишут, что вроде как это результат одного из взломов Rockstar со стороны хакеров. Как, вероятно, думал хакер: игру все ждут, а проклятая студия скрывает подробности разработки. Покажу всем фанатам, чтобы они хоть какую-то инфу получили! Что получилось на деле: студия, вероятно, вынуждена будет переделывать некоторые куски, которые уже слиты, чтобы оставить в сюжете и механиках интригу. К тому же, дополнительные ресурсы сейчас ещё и уйдут на усиление внутренней безопасности, поиск кротов и так далее. Атмосфера в командах разработки из-за этого тоже ухудшится. Срок выхода игры отодвинется. Неизвестно, надолго ли, но точно это на срок повлияет. Фанатам игры, которые её ждут, станет хуже. Впрочем, всегда есть вероятность, что хакер просто ненавидит корпорации, на игру ему плевать, он просто хотел сделать плохо Rockstar. Кстати, если бы, грубо говоря, фанаты договорились не смотреть видео и не пересылать его друг другу, ущерб студии был бы куда меньше, и игра вышла бы скорее. Эта идея в несколько другой форме была в самой первой серии первого сезона Black Mirror (да, про свинью). #games

Hashtags

Резултати

Намерени 3 подобни публикации

Търсене: #eotc

当前筛选 #eotc清除筛选
Borkena

@borkena · Post #5891 · 28.02.2026 г., 17:14

አባ ሳዊሮስ በአርሲ በደረሰው የምዕመናን ግድያ ሀዘናቸውን ገለፁ። የሀዘን መግለጫ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሽርካ ወረዳ በጃዊ ቀበሌ 21 ኦርቶዶክሳውያን በታጣቂዎች ሕይወታቸው ማለፉን ተከትሎ የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን እንገልጻለን። በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሽርካ ወረዳ በጃዊ ቀበሌ በታጣቂዎች ጥቃት የካቲት 19 ለ 20 አጥቢያ አንድ ካህን፣ ሁለት ሴቶች እና 18 ወንድ ኦርቶዶክሳውያን በግፍ መገደላቸውን የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ለጽሕፈት ቤታችን ከጻፉት ደብዳቤ ስንመለከት እጅግ በከፍተኛ ኀዘን ተሰምቶናል። በመሆኑም በሀገረ ስብከቱ በተለያዩ ጊዜያት በኦርቶዶክሳዊያን ልጆቻችን ላይ የሚፈጸመውና የተፈጸመው ዘግናኝና እጅግ አሳዛኝ ግድያዎች የኦርቶዶክሳዊያን ልጆቻችንን በየትኛውም የአገራችን ክፍል በነጻነት የመኖርና ሃይማኖታዊ ሥርዓታቸውን የመፈጸም መብትን የሚጋፋ በመሆኑ የክልሉና የፌዴራል መንግሥታት ጉዳዮን በልዩ ሁኔታ መከታተልና የማያዳግም መፍትሔ የሚያገኝበት መንገድ መፈለግ እንዳለባቸው እያሳሰብን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትም የአካባቢው ችግር በመሰረቱ እስከሚፈታ ድረስ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በዚህ አጋጣሚ ለመግለጽ እንወዳለን። በመጨረሻም በዚህ ዘግናኝና አሳዛኝ ግድያ ሕይወታቸውን ላጡ ልጆቻችን እግዚአብሔር አምላክ መንግሥተ ሰማያትን እንዲያወርስልን እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸውም መጽናናትን እንዲሰጥልን የቅድስት ቤተክርስቲያናችን የዘወትር ጸሎቷ መሆኑን እንገልጻለን። አባ ሳዊሮስ #Ethiopia#Oromiyaa#ArsiZone#ethiopianorthodoxtewahedochurch#EOTC

Borkena

@borkena · Post #5897 · 01.03.2026 г., 16:36

ሲኖዶሱ በአርሲ የደረሰውን ጥቃት አወገዘ። ​ በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ አርሲ የተፈጸመው የንጹሐን ግድያ ለዘመናት የዘለቀውን የሃይማኖቶች ተከባብሮ የመኖር እሴት ለመናድ የታለመ ነው ሲል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ድርጊቱን በጽኑ አውግዟል። በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በተለያዩ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ እየተፈጸመ ያለው ጥቃት በአዲስ መልክ ቀጥሎ የ21 ንጹሐን ወገኖች ሕይወት በግፍ ማለፉን ቋሚ ሲኖዶስ በመሪር ኃዘን ገልጿል። ኦርቶዶክሳውያን በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በነፃነት የመኖርና ሥርዓተ አምልኮ የመፈጸም ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸው ሊከበር ይገባል ያለው ቋሚ ሲኖዶሱ፤ የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት እርምጃዎች በአፋጣኝ እንዲወስዱ አሳስቧል። በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ያለው ሞትና መፈናቀልም ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን በየትኛውም የሀገራችን ክፍል በነጻነት ሠርተው የመኖርና ሥርዓተ አምልኮ የመፈጸም ሕገ መንግሥታዊ መብታቸውን የሚጋፋ በመሆኑ የክልሉና የፌዴራል መንግሥት ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ ተከታትለው አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡበት ቋሚ ሲኖዶስ በጥብቅ ያሳስባል፣እንዲሁም ለተፈጸመው ግፍ አፋጣኝ ፍትሕ እንዲሰጥና ገዳዮች በሕግ እንዲጠየቁ እና የዜጎችን ደኅንነትና ንብረት የማስጠበቅ የመንግሥት ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ፤የሀገር ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ዐቢይ ኮሚቴ ከመንግሥት ጋር በመነጋገር ዘላቂ መፍትሔ እንዲያመጣ ቋሚ ሲኖዶስ አሳስቧል ። ​በመጨረሻም ቋሚ ሲኖዶስ ስለስሙ መከራን ለተቀበሉ" ንጹሐን ዕረፍተ ነፍስን፣ ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን ተመኝቷል። #Ethiopia#AddisAbaba#Oromia#EOTC#Arsi#Ethiopiannews#ዜና#አርሲ