@ebcnewsnow · Post #53588 · 16.04.2026 г., 03:50
"ምንም ጥርጥር የለውም፤ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዐሥር ዓመታት በአፍሪካ ውስጥ አውራ ሀገር ትሆናለች" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) Ethiopian Broadcasting Corporation #Ethiopia#ebcdotstream
Hashtags
TGINSIGHT SIMILAR POSTS
Изходен канал @clockstackwheels · Post #867 · 17.09
Платформа для разработки игр Unity в своё время совершила революцию. Это, кстати, хороший способ запустить успешный проект: нужно с помощью цифровизации упростить какой-то сложный процесс. Например, Uber упростил заказ такси, Arduino упростил вхождение в любительскую электронику, Тинькофф упростил многие банковские операции и так далее. Вот Unity значительно упростил работу с игровыми движками — сделал простой и логичный конструктор поверх движка, который позволил создавать объекты, анимации, задавать физические параметры и так далее. Это было настолько нужным и удачным решением, что половина игровой индустрии, кроме дорогих высокобюджетных проектов, с тех пор подсела на Unity. Инди-игры и мобильные игры практически целиком на нём, и даже некоторые AAA-компании активно его юзают: например, на нём сделан Hearthstone. И вот несколько дней назад компания объявила, что с 2024 года начнёт взимать с разработчиков деньги за каждую установку каждой игры (до этого были разные уровни платной подписки на движок). Ну, то есть, у тебя уже написан огромный и дорогой проект на движке, существующий много лет, и автор движка, как оказалось, имеет право в какой-то момент сказать: плати мне миллионы долларов или отключай свой проект. Для многих это не просто удар, это полный крах всего бизнеса, построенного на играх. Здесь можно было бы понудеть ещё раз о зависимости от корпораций, но любопытно другое. Игровая индустрия поехала массово хоронить и бойкотировать Unity, а само решение действительно кажется предельно абсурдным. Unity и так зарабатывал очень много, причем, для поддержки движка не нужны значительные траты. Выяснилось, что члены совета директоров, и даже сам генеральный, за последние пару лет продали десятки тысяч своих акций Unity, а новых не купили. Это реально по куче признаков выглядит, как убийство компании изнутри и попытка дожать остатки. Говорят, что проект решил не ввязываться в конкуренцию с растущим по популярности Unreal Engine, у которого вроде как появляется вменяемый инструментарий для людей. Если студии, которые сейчас выражают протесты, не сольются и массово откажутся от использования движка, то коллективно они вполне могут обвалить Unity. Хорошее в этом тоже есть: надеюсь, что подобные события стимулируют развитие опенсорсной альтернативы — Godot. #dev#games
Търсене: #ebcdotstream
@ebcnewsnow · Post #53588 · 16.04.2026 г., 03:50
"ምንም ጥርጥር የለውም፤ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዐሥር ዓመታት በአፍሪካ ውስጥ አውራ ሀገር ትሆናለች" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) Ethiopian Broadcasting Corporation #Ethiopia#ebcdotstream
Hashtags
@ebcnewsnow · Post #53310 · 11.04.2026 г., 07:37
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ************ የአፍሪኤግዚም ባንክ ፕሬዝደንት የሆኑትን ዶክተር ጆርጅ ኢሎምቢን ዛሬ ተቀብያለሁ። በነበረን የጋራ ቆይታ፣ ስትራቴጂካዊ ግንኙነታችንን በምናጠናክርባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገናል። #EBC#ebcdotstream#Ethiopia
Hashtags
@ebcnewsnow · Post #52443 · 18.03.2026 г., 02:59
"በከተሞቻችን እንደ ውኃ፣ መብራት፣ የፍሳሽ መሠረተ ልማት፣ ጤና እና ትምህርት መሠረታዊ ፍላጎቶችን በጥራት ማቅረብ የመደመር መንግሥት አንዱ ግብ ነው። የከተሞች ጸጥታና ደኅንነት ከዕድገታቸው እና ከግባቸው ጋር መመጣጠን አለበት። በተጨማሪም የከተሞች ክፍሎች የንግድ አካባቢ፣ የመኖሪያ አካባቢ እና የመኖሪያ አካባቢ ተብለው ተለይተው መገንባት አለባቸው። ይህም መሠረተ ልማትን፣ አገልግሎትን እና የሕዝብ ፍላጎትን ያሣልጣል።" የመደመር አንቀፅ ገፅ 237 #EBC#Ethiopia#EBCDOTSTREAM
Hashtags
@ebcnewsnow · Post #51260 · 25.01.2026 г., 07:38
ባንኮች ለተመረጡ የገቢ ዕቃዎች የጉምሩክ ዋጋን እንደ አመላካች ዋጋ እንዲጠቀሙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ ************************ ባንኮች ለተመረጡ የገቢ ዕቃዎች የብድር ሰነድ (Letters of Credit) ይሁን ሌላ ክፍያ መንገድ ሲፈቅዱ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ተመንን እንደ አመላካች ዋጋ እንዲጠቀሙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሐምሌ 2016 ዓ.ም ተግባራዊ ያደረገውን የውጭ ምንዛሪ መመሪያን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን በገበያ እንዲወሰን መደረጉ ይታወቃል። መመሪያው ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር በመደራደር የውጭ ምንዛሪ መሸጫ እና መግዣ ተመኖችን መወሰን እንዲችሉ ይፈቅዳል። በተጨማሪም ባንኮች ቀደም ሲል ይጠቀሙበት የነበረው ዝቅተኛ የገቢ ዕቃዎች ዋጋ መመሪያ (Minimum Price Directive) በመሰረዙ፤ አሁን ግን በአዲሱ የውጭ ምንዛሪ መመሪያ መሠረት የገቢ የዕቃዎችን ዋጋ ትክክለኝነት የማረጋገጥ ኃላፊነት አለባቸው። ይሁን እንጂ፣ ባንኮች ለብድር ሰነድ (Letters of Credit) የሚጠቀሙባቸው ዋጋዎች ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የማጣቀሻ ዋጋዎች ጋር ሲነፃፀሩ ከፍተኛ ልዩነት እንዳላቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባደረገው ክትትል አረጋግጧል። በመሆኑም የዋጋ ልዩነቶቹን ለማስተካከልና የዋጋ ማጣቀሻዎችን ለማጣጣም ሁሉም ባንኮች ከጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም (January 27, 2026) ጀምሮ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ተመንን እንደ አመላካች ዋጋ ይጠቀማሉ። ይህም በባንክ ሥርዓቱ እና በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን መካከል ያለውን የዋጋ ልዩነት ለማስወገድ እና የውጭ ምንዛሪ መረጃዎችን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። #EBC#ebcdotstream#Ethiopia
Hashtags
@ebcnewsnow · Post #51788 · 19.02.2026 г., 08:39
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሁለተኛው ክርክር በኢቢሲ በቅርብ ቀን ይጠብቁን! ብልጽግና ፓርቲ አማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እናት ፓርቲ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ፓርቲ በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የተደረገ ሁለተኛው የምርጫ ክርክር በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን። በምርጫ ብቻ!! #ethiopianbroadcastingcorporation#EBCDOTSTREAM
@ebcnewsnow · Post #51614 · 12.02.2026 г., 17:11
የምርጫ 2018 የፖለቲካ ፓርቲዎች የመጀመርያ ክርክር በኢቢሲ በቅርብ ቀን ይጠብቁን! ብልጽግና ኢዜማ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ነፃነትና እኩልነት በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የተደረገ የመጀመሪያ የምርጫ ክርክር በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን። በምርጫ ብቻ!! #ethiopianbroadcastingcorporation #EBCDOTSTREAM
@ebcnewsnow · Post #51565 · 09.02.2026 г., 16:59
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የሰው አልባ ፖሊስ አገልግሎት በይፋ አስጀመሩ ************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የሰው አልባ ፖሊስ አገልግሎት ወይም ስማርት ፖሊስ አገልግሎት በይፋ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው፤ ዛሬ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የሰው አልባ ፖሊስ አገልግሎት ወይም ስማርት ፖሊስ አገልግሎት አስጀምረናል ብለዋል። ይህ አገልግሎት ዜጎች የፖሊስ አገልግሎትን በተሻለ ፍጥነት እና በቴክኖሎጂ ታግዘው እንዲያገኙ እንደሚያስችል ገልፀዋል። በተጨማሪም አገልግሎቱ ለፖሊስ ፈጣን እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችለው እና የወንጀል መከላከል ስራውን የሚያቀላጥፍ መሆኑን ጠቅሰዋል። የዚህ አገልግሎት መጀመር በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የህግ አስከባሪ አካላት ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የተጀመረው የሪፎርም ስራን ውጤታማነት የሚያሳድግ ይሆናል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልእክታቸው። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia
@ebcnewsnow · Post #51212 · 23.01.2026 г., 13:44
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአየር ኃይል 90ኛ ዓመት የአቪዬሽን ኤክስፖን ጎበኙ ***************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የኢፌዲሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ በተሰናዳው የአቪዬሽን ኤክስፖ 2026 ይፋዊ የመክፈቻ መርሃግብር ላይ ተገኝተዋል። ኤክስፖው “የወደፊቱን የአቬሽን አቅም በጋራ እንገባ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ሲሆን ኢትዮጵያ ለአቪዬሽን እና ኤሮስፔስ ልማት፣ አለም አቀፍ ትብብርን በማጠናከር እና ሀገራችንን በአቪዬሽን ልማት የቀጣናው እና አኅጉሩ የፈጠራ፣ የክህሎት ልማት እና የዘላቂ እድገት ማዕከል ማድረግ ላይ ያላትን ጽኑ አቋም እና ተግባር ያሳያል። #PMOEthiopia#EBC#ebcdotstream
Hashtags
@ebcnewsnow · Post #51543 · 08.02.2026 г., 12:49
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ሥራ ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ ሰራተኞች ማዕድ አጋሩ ***************** ዛሬ በ24/7 የሥራ ባሕል የከተማችንን የኮሪደር ልማት ሥራዎች እያፋጠኑ ከሚገኙ ታታሪ ሰራተኞች ጋር ማዕድ በማጋራት አበረታተናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ እነዚህ ብርቱ ሰራተኞች በተለያዩ የግንባታ ሳይቶች፤ በተለይም በካዛንቺስ የሕፃናት ዓለም፣ በስፖርት ፓርክ እና በአዲስ አኳሪየም ግንባታዎች፣ እንዲሁም ከኡራኤል እስከ ቦሌ ቪ.አይ.ፒ፣ ከኢንግሊዝ ኢምባሲ 22 እስከ ቦሌ ፍሬንድሺፕ ሆቴል እና ከውኃ ልማት እስከ ቦሌ ሩዋንዳ አካባቢ እየተከናወኑ ባሉ መጠነ ሰፊ የኮሪደር ልማት አያያዥ መስመሮች ላይ ሌት ተቀን የሚተጉ ናቸው ብለዋል። በከፍተኛ የአገር ፍቅር ስሜት ለከተማችን ሁለንተናዊ ዕድገት በእውቀታቸውና በጉልበታቸው እያበረከቱ ላለው አስተዋፅኦ ከልብ እናመሰግናለን፤ አዲስ አበባ ሁልጊዜም ታመሰግናችኋለች ሲሉም ገልፀዋል። በከተማችሁ መልማት በመደሰት ሁሌ በማዕድ ማጋራት እና እነዚህን ብርቱ ሰራተኞ በማበረታት መርኃ ግብር እየተሳተፋችሁ ላላችሁ ባለሀብቶች በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል ከንቲባዋ በመልእክታቸው። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#AddisAbaba
@ebcnewsnow · Post #52009 · 03.03.2026 г., 13:35
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ያደረጉት ቆይታ! ዛሬ ምሽት 2:30 ይጠብቁን! #EBC#ebcdotstream#Ethiopia#AbiyAhmed
@ebcnewsnow · Post #51848 · 21.02.2026 г., 18:12
የኮሪደር ልማት ስራዎች በርካታ ከተሞችን እየለወጡ ይገኛሉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ****************** የኮሪደር ልማት ስራዎች የተሻለ ሀገርን ለትውልድ የመገንባት አካል ሆነው በርካታ ከተሞችን እየለወጡ ይገኛሉ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት፤ በሐዋሳ ከተማ በሁለተኛው ምዕራፍ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በዛሬው ዕለት ተመልክተናል ብለዋል። የኮሪደር ልማት ስራዎች የተሻለ ሀገርን ለትውልድ የመገንባት አካል ሆነው በርካታ ከተሞችን እየለወጡ ይገኛሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አጠቃላይ ስራዎቹ እያደገ ለመጣው ከተሜነት ሀገርን ያዘጋጁ መሆናቸውንም ገልፀዋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#PMAbiy
@ebcnewsnow · Post #51684 · 14.02.2026 г., 11:44
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦካይ ጋር መከሩ ***************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦካይ ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ ከላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ቦካይ ጋር ተገናኝተን በቴክኖሎጂ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና በተለይም ኢትዮጵያ ለመመስረት ባቀደችው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ በተመለከተ የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል ብለዋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#PMAbiy