TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← Аниме,Музыка, Аниме эдиты

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Find similar content

Source channel @StickerEdit · Post #5721 · Apr 29

Аниме: #БлюЛок Тип: #Авы

Results

1 similar post found

Search: #historicalright

当前筛选 #historicalright清除筛选
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)

@ebcnewsnow · Post #52023 · 03/04/2026, 11:08 AM

ከአሰብ ደጃፍ ላይ ሆነው የባሕር በር የሚናፍቁት የሱልጣን አሊ ሚራህ ልጆች ************ አፋሮች ከአባቶቻቸው የወረሱትን ኢትዮጵያዊነትና የቀይ ባሕር ባለቤትነት መንፈስ ይዘው፣ በሴራ ያጣነውን የባሕር በር በሰለጠነ ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማስመለስ በጽናት እንደሚታገሉ አስታወቁ። የአፋር ህዝብ ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ትስስር ጥንታዊና የማይበጠስ መሆኑን የገለጹት የኤሊ ዳአር ወረዳ የሀገር ሽማግሌዎችና ነዋሪዎች፣ የቀይ ባሕር በር ለሀገር ህልውና ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። የሀገር ሽማግሌ አቶ መሐመድ አብደላ ከኤሊ ዳአር ወረዳ፣ "አፋርነት ከኢትዮጵያዊነት ጋር የተገመደ የጥንት ማንነት ነው። ሱልጣን አሊ ሚራህ አንፈሬ 'አፋር አፋር ነው፤ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ ግመሎቹም የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ለይተው ያውቃሉ' ሲሉ የገለጹት ይኸው የማይበጠስ ትስስር ነው። ሱልጣኑ ኢትዮጵያ የባሕር በሯን እንዳታጣ የከፈሉት ታላቅ መስዋዕትነት ዛሬም በትውልዱ ልብ ውስጥ ህያው ሆኖ ጥያቄው ሳይበርድ ይኖራል ብለዋል የወረዳው ነዋሪዎች። ዛሬም ከአሰብ ደጅ ከኤሊ ዳአር ሆነን የምናውጀው አንድ እውነት አለ፤ ቀይ ባሕር ታሪካዊ አካል የሁላችንም ኩራት ነው በማለት ተናግረዋል፡፡ አፋር ያለ ኢትዮጵያ አይኖርም። ቀይ ባሕር የኛ ነው፣ እኛ የኢትዮጵያ ነን።" በማለት የአፋርን የማይነጣጠል የኢትዮጵያዊነት ትስስር ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በርን ለማስመለስ ለምታደርገው ዲፕሎማሲያዊ ትግል የአፋር ህዝብ እንደሚደግፍ እና ለውጤት እንዲበቃ እንደሚሰራም አቶ መሐመድ አብደላ አረጋግጠዋል። በላሉ ኢታላ #Ethiopia#RedSea#HistoricalRight#Geopolitics#MaritimeLaw#NationalInterest#Africa