@ebcnewsnow · Post #51262 · 01/25/2026, 10:14 AM
“የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኢትዮጵያን ለመድፈር ለሞከሩ ኃይሎች ሁነኛ መድኃኒት ሆኖ ሀገር ያጸና ተቋም ነው።” - የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #PMOEthiopia#ETAF90
Hashtags
TGINSIGHT SIMILAR POSTS
Source channel @githubtrending · Post #14913 · Jul 3
#typescript#boilerplate#boilerplate_code#jamstack#javascript#js_boilerplate#netlify_template#next_js#next_theme#nextjs#nextjs_starter#nextjs_template#react#react_boilerplate#reactjs#starter_kit#starter_project#starter_template#tailwind_css#tailwindcss#typescript You can quickly start a modern web project using a ready-made Next.js boilerplate that includes the latest Next.js 15 features, Tailwind CSS 4, and TypeScript. It offers built-in user authentication, multi-language support, type-safe database tools, error monitoring, AI code reviews, and security features like bot protection. The setup is easy with local and remote database options, automatic testing, and deployment guides. This saves you time and effort by providing a flexible, production-ready foundation with best practices, letting you focus on building your app instead of configuring tools and infrastructure. It also supports smooth development with live reload and VSCode integration. https://github.com/ixartz/Next-js-Boilerplate
Search: #etaf90
@ebcnewsnow · Post #51262 · 01/25/2026, 10:14 AM
“የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኢትዮጵያን ለመድፈር ለሞከሩ ኃይሎች ሁነኛ መድኃኒት ሆኖ ሀገር ያጸና ተቋም ነው።” - የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #PMOEthiopia#ETAF90
Hashtags
@ebcnewsnow · Post #51274 · 01/25/2026, 08:58 PM
የጠላት ጄቶችን አየር ላይ ያጋጩት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ - ብርጋዴር ጄኔራል ለገሰ ተፈራ! 🇪🇹✈️ ************ ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷን አስከብራ የኖረችው እንደ ብርጋዴር ጄኔራል ለገሰ ተፈራ ባሉ የማይበገሩ ጀግኖች መስዋዕትነት ነው። የአየር ኃይላችን የ90 ዓመት ጉዞ ሲታሰብ፣ የነዚህ "የሰማይ ንስሮች" ታሪክ ምንጊዜም በደማቁ ይነሳል። የጄኔራል ለገሰ አስደናቂ የጀግንነት ታሪክ፦ 💥 የአየር ላይ ጀብዱ፦ በኢትዮ-ሶማሊያ ጦርነት ወቅት (1969-70 ዓ.ም) ‘F5-E' የጦር ጄትን በማብረር፣ 2 የጠላት ‘ሚግ 21' ጄቶችን አየር ላይ እርስ በርስ እንዲጋጩ በማድረግና ሌሎች በርካታ ጄቶችን በመጣል የማይረሳ ታሪክ ሠርተዋል። 📚 የታሪክ ምስክርነት፦ ኦስትሪያዊው የታሪክ አጥኚ ቶም ኩፐር ‘Wings over Ogaden' በተሰኘ መጽሐፉ፤ የኢትዮጵያ አብራሪዎች በቁጥር ቢበለጡም በላቀ ክህሎታቸው ፍጹም የአየር ላይ የበላይነት እንደነበራቸው መስክሯል። 💪 ጽናትና መስዋዕትነት፦ በድሉ ዋዜማ በፊልቱ ግንባር ጄታቸው ተመትታ በፓራሹት ወርደው በጠላት እጅ ወደቁ። ይህን ተከትሎ ለ11 ዓመታት በሶማሊያ እስር ቤት አሰቃቂ ስቃይ ቢደርስባቸውም፤ ይህ ለሀገራቸው የነበራቸውን ፍቅር ሊያጠፋው አልቻለም። 🏅 የክብር ሽልማት፦ ከእስር ተመልሰው ሀገራቸው ሲገቡ በወቅቱ የሀገሪቱ ከፍተኛ የክብር ሽልማት የነበረውን "የኅብረተሰብዓዊት ኢትዮጵያ ወደር የለሽ ጀግና ሜዳይ" ተሸልመዋል። ዛሬም የአየር ኃይላችን ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ታጥቆ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ሲቆም፣ የእነዚህ ጀግኖች ታሪክ ለትውልዱ ትልቅ የሞራል ስንቅ ነው። #EBCDotstream#Ethiopia#EthiopianAirForce#LegesseTefera#Hero#AviationHistory#ETAF90#NationalPride#MilitaryExcellence ሙሉ ዘገባውን እዚህ ያገኙታል።