TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← GitHub Trends

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Find similar content

Source channel @githubtrending · Post #14980 · Jul 20

#html#hacktoberfest CSS exercises help you practice styling web pages by editing HTML and CSS files to match given designs. You can use resources like documentation and Google to complete them, which builds your real-world skills without needing to memorize everything. Practicing this way improves your understanding of CSS, making it easier to create visually appealing, user-friendly websites that load faster and work well on different devices. It also helps you learn how to organize and update styles efficiently, which is important for web development jobs. Using git to save your work encourages good coding habits. This hands-on practice boosts your confidence and prepares you for real projects[1][2][3][4]. https://github.com/TheOdinProject/css-exercises

Results

1 similar post found

Search: #generaltadessewerede

当前筛选 #generaltadessewerede清除筛选
Borkena

@borkena · Post #5819 · 02/21/2026, 09:49 AM

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መከላከያ ወደ ትግራይ ይገባል መባሉን አስተባበለ። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ጽሕፈት ቤት ዛሬ የካቲት 14/2018 ዓ. ም ባወጣው መግለጫ፣ መከላከያ ሠራዊት በትግራይ ክልል በሚገኙ የቀድሞው የሰሜን ዕዝ ካምፖች እንዲሰፍር አለመስማመቱን አስታውቋል፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ወደ ትግራይ ክልል እንዲገባ በፌደራል መንግሥት ትዕዛዝ ተላልፏል በሚል የተሰራጨው መረጃ ሐሰት ነው በማለት ውድቅ አድርጓል፡፡ ባለፉት ቀናት የፌደራል መንግሥት መከላከያ ሠራዊት ወደ ትግራይ ክልል እንደሚገባ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ማሳወቁን የሚገልጹ መረጃዎች ወጥተዋል። ሰራዊቱ በክልሉ የሚገኙ ካምፖችን መልሶ እንዲቆጣጠርና ኤርትራን በሚያዋስኑ ድንበሮች ላይ እንድሰፍር ትዕዛዝ ተላልፏል ተብሏል። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ በጉዳዩ ላይ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ለማስፈጸም መስማማታቸውም ተመላክቷል። ነገርግን ጽሕፈት ቤቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ዕዝ ካምፖች እንዲሰፍር ተስማምቷል መባሉን ሙሉ በሙሉ አስተባብሏል፡፡ ይሁን መረጃ የተሰማው የፌደራል መንግስት በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኘውን ጦር አሰባስቦ ወደትግራይ እያስገባ ነው በሚባልበት ወቅት ነው። ባሳለፍነው ሳምንት የፀጥታ ችግር የተከሰተበትና የ20 ሰዎች ህይወት ያለፈበት የጋሞ ዞን ግጭት መንስዔው፣ መከላከያ ከአካባቢው ወጥቶ ወደ ትግራይ ክልል በመሄዱ መሆኑን ስማቸው እንድገለፅ ያልፈለጉ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አመራር በወቅቱ ተናግረዋል። #Ethiopia#Tigray#ENDF#AbiyAhmed#GeneralTadesseWerede