TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← GitHub Trends

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Find similar content

Source channel @githubtrending · Post #15071 · Aug 18

#typescript#agent#agentic_ai#agents#ai#ai_agents#ai_tools#anthropic#automation#bytebot#computer_use#computer_use_agent#cua#desktop#desktop_automation#docker#gemini#llm#mcp#openai Bytebot is an open-source AI desktop agent that acts like a virtual employee with its own computer, able to use real applications, browse websites, handle passwords, and process documents automatically. You just describe tasks in plain English, and Bytebot completes them by clicking, typing, downloading files, organizing data, and running complex workflows across multiple programs. It runs locally on your own infrastructure, ensuring privacy and full control, and supports many AI models. This helps you save time by automating repetitive or complex tasks without scripting, improving efficiency and accuracy in business, research, or development work. https://github.com/bytebot-ai/bytebot

Results

1 similar post found

Search: #generaltadessewerede

当前筛选 #generaltadessewerede清除筛选
Borkena

@borkena · Post #5819 · 02/21/2026, 09:49 AM

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መከላከያ ወደ ትግራይ ይገባል መባሉን አስተባበለ። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ጽሕፈት ቤት ዛሬ የካቲት 14/2018 ዓ. ም ባወጣው መግለጫ፣ መከላከያ ሠራዊት በትግራይ ክልል በሚገኙ የቀድሞው የሰሜን ዕዝ ካምፖች እንዲሰፍር አለመስማመቱን አስታውቋል፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ወደ ትግራይ ክልል እንዲገባ በፌደራል መንግሥት ትዕዛዝ ተላልፏል በሚል የተሰራጨው መረጃ ሐሰት ነው በማለት ውድቅ አድርጓል፡፡ ባለፉት ቀናት የፌደራል መንግሥት መከላከያ ሠራዊት ወደ ትግራይ ክልል እንደሚገባ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ማሳወቁን የሚገልጹ መረጃዎች ወጥተዋል። ሰራዊቱ በክልሉ የሚገኙ ካምፖችን መልሶ እንዲቆጣጠርና ኤርትራን በሚያዋስኑ ድንበሮች ላይ እንድሰፍር ትዕዛዝ ተላልፏል ተብሏል። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ በጉዳዩ ላይ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ለማስፈጸም መስማማታቸውም ተመላክቷል። ነገርግን ጽሕፈት ቤቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ዕዝ ካምፖች እንዲሰፍር ተስማምቷል መባሉን ሙሉ በሙሉ አስተባብሏል፡፡ ይሁን መረጃ የተሰማው የፌደራል መንግስት በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኘውን ጦር አሰባስቦ ወደትግራይ እያስገባ ነው በሚባልበት ወቅት ነው። ባሳለፍነው ሳምንት የፀጥታ ችግር የተከሰተበትና የ20 ሰዎች ህይወት ያለፈበት የጋሞ ዞን ግጭት መንስዔው፣ መከላከያ ከአካባቢው ወጥቶ ወደ ትግራይ ክልል በመሄዱ መሆኑን ስማቸው እንድገለፅ ያልፈለጉ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አመራር በወቅቱ ተናግረዋል። #Ethiopia#Tigray#ENDF#AbiyAhmed#GeneralTadesseWerede