TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← GitHub Trends

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Find similar content

Source channel @githubtrending · Post #15321 · Dec 9

#go#game_engine#game_engine_2d#game_engine_3d#game_engine_development#game_engine_framework#gameengine#go#golang Kaiju Engine is a fast, modern 2D/3D game engine written in Go and powered by Vulkan, designed for simplicity and high performance. It runs on Windows, Linux, Android, and is working on Mac support. Kaiju offers much faster rendering speeds and lower memory use than popular engines like Unity, making game development quicker and more efficient. It uses Go’s garbage collector to help prevent common programming errors, improving stability. You can write games directly in Go, and the engine supports local AI integration and a flexible UI system using HTML/CSS. Although the editor is still in development, the engine itself is production-ready, offering a powerful tool for developers who want speed and simplicity. https://github.com/KaijuEngine/kaiju

Results

2 similar posts found

Search: #nationalid

当前筛选 #nationalid清除筛选
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)

@ebcnewsnow · Post #51455 · 02/02/2026, 07:44 PM

የፋይዳ መታወቂያን በ"PDF" አውርዶ የመያዝ አማራጭ በጊዜያዊነት ለምን ተቋረጠ? ********************* የፋይዳ መታወቂያን በ"PDF" አውርዶ የመያዝ አማራጭ በጊዜያዊነት መቋረጡን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ። ይህ የተደረገበት ምክንያትም፦ • በየአካባቢው የሚገኙ የኢንተርኔት እና ህትመት ቤቶች ጥራት በሌላቸው ካርዶች እያተሙ በመሆኑ • የአንድን ግለሰብ ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ በፎቶሾፕ እያስመሰሉ በመሥራት የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎችን እያጭበረበሩ ያሉ አታሚዎች በስፋት በመታየታቸው • ከከተማ ራቅ ብለው የሚኖሩና በቂ ግንዛቤ የሌላቸው ዜጎች ትክክለኛ ባልሆነ የካርድ ህትመት እየታለሉ፤ በዚህም ገንዘብ እና ጊዜያቸውን ከመጭበርበራቸው ባሻገር የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት እንዳይችሉ እያደረገ በመሆኑ ነው ብሏል። ስለዚህ ዜጎች የኢሌክትሮኒክ ፋይዳ (ኢ-ፋይዳ) አማራጭ ሲፈልጉ ከ"Fayda ID" ሞባይል መተግበሪያ በቀላሉ ማግኘት እንደሚችሉ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል። #Ethiopia#NationalID#Fayda#EthiopianBroadcastingCorporation

EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)

@ebcnewsnow · Post #51344 · 01/29/2026, 11:39 AM

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ብራንድ አምባሳደር ሆነ ************** የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም በአትሌቲክስ በተለያዩ ርቀቶች የዓለም ሪከርድ ባለቤት የሆነውን አትሌት ቀነኒሳ በቀለን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ብራንድ አምባሳደር አድርጓል። አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ የተሰየመው፣ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የፋይዳ አምባሳደር ይፋዊ ሥራ ማስጀመሪያ መርኃ ግብርን ባካሄደበት ወቅት ነው። የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ፋይዳን ለሁሉም ለማድረስ የ100 ፐርሰንት ዕቅድ አቅዷል፡፡ እስካሁን ከ32 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የመታወቂያው ባለቤት መሆናቸውና በበጀት ዓመቱም ለ 90 ሚሊዮን ዜጎች ለማድረስ ዕቅድ መያዙ ተገልጿል። ይህን ግብ ለመደገፍም ታዋቂ እና በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያለው የብራንድ አምባሳደር መሰየም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ አትሌት ቀነኒሳን ብራንድ አምባሳደር ማድረጋቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ አቶ ዮዳሄ አርዓያስላሴ ተናግረዋል። አቶ ዮዳሄ አክለውም፤ አትሌቱ በሕዝብ ዘንድ ያለውን ተቀባይነት እና ተወዳጅነት በመጠቀም በሁሉም የሀገሪቱ ከፍሎች ያሉ ነዋሪዎችን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ ለማድረግ በጋራ እንደሚሰራም ገልጸዋል። አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በበኩሉ፤ ሀገራዊ ፋይዳ ላለው ፕሮጀከት ብራንድ አምባሳደር ሆኖ በመመረጡ ክብር እንደሚሰማው ተናግሯል። የፋይዳ አምባሳደር አትሌት ቀነኒሳ በቀለ፤ በአምባሳደርነት ቆይታው የተለያዩ የቴለቪዥን፣ የማህበራዊ ሚዲያ፣ የቢልቦርድ ማስታወቂያዎች ላይ መሳተፍ እንዲሁም የተለያዩ ኩነቶች ላይ በመገኘትና ንግግር በማድረግ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በተመለከተ የማስተዋወቅ ተግባራትን እንደሚያከናውን ይጠበቃል። በፍሬህይወት ረታ #EthiopianBroadcastingCorporation#Ethiopia#DigitalID#fayda#NationalID#DigitalEthiopia