TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← GitHub Trends

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Find similar content

Source channel @githubtrending · Post #15321 · Dec 9

#go#game_engine#game_engine_2d#game_engine_3d#game_engine_development#game_engine_framework#gameengine#go#golang Kaiju Engine is a fast, modern 2D/3D game engine written in Go and powered by Vulkan, designed for simplicity and high performance. It runs on Windows, Linux, Android, and is working on Mac support. Kaiju offers much faster rendering speeds and lower memory use than popular engines like Unity, making game development quicker and more efficient. It uses Go’s garbage collector to help prevent common programming errors, improving stability. You can write games directly in Go, and the engine supports local AI integration and a flexible UI system using HTML/CSS. Although the editor is still in development, the engine itself is production-ready, offering a powerful tool for developers who want speed and simplicity. https://github.com/KaijuEngine/kaiju

Results

1 similar post found

Search: #proclamation

当前筛选 #proclamation清除筛选
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)

@ebcnewsnow · Post #53835 · 04/21/2026, 01:26 PM

የፌዴራል የስፖርት ልማት እና አስተዳደር አዋጅ በሙሉ ድምፅ ጸደቀ ********************* የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ፣ የስፖርት ዘርፍ ላይ መሠረታዊ ለውጥ ያመጣል ተብሎ የታመነበትን የፌዴራል የስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አጽድቋል። አዲሱ አዋጅ ቁጥር 1413/2018 በስፖርቱ ዘርፍ አካታች፣ ዘመናዊና ግልጽነት ያለው የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት ምቹ መደላድል የሚፈጥር ሲሆን፣ በዘርፉ የሚታዩ የአሰራርና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ታላቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል። አዋጁ የስፖርት መሠረተ ልማቶችንና ማሰልጠኛ ተቋማትን ከማስፋፋት ባለፈ፣ የስፖርት ግብዓት አምራቾች እንዲበረታቱና ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የራሱን ድርሻ እንዲያበረክት ያደርጋል። በተጨማሪም ማህበራዊ ትስስርን በማጎልበት፣ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን በማጠናከር እና ስፖርት ነክ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚጫወት በምክር ቤቱ የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ አብራርተዋል። የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በሰጡት ማብራሪያ፣ ስፖርት የኢትዮጵያውያን የኩራት ምንጭ እንዲሆን ዘርፉን የያዙ ማነቆዎችን በአሰራርና በስርዓት መፍታት የግድ እንደሚል ጠቁመዋል። አዋጁ ከዘርፉ ማግኘት ያለባትን ጥቅም እንድታገኝ በማድረግ ረገድ መሠረታዊ ለውጥ እንደሚያመጣ ሚኒስትሯ ገልጸዋል። የምክር ቤቱ አባላትም የአዋጁን አስፈላጊነት በማመንና አፈጻጸሙ ላይ ትኩረት እንዲደረግ በማሳሰብ አዋጁን በሙሉ ድምፅ ማጽደቁን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ethiopia#SportsDevelopment#Parliament#Proclamation#EthiopianSports