TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← GitHub Trends

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Find similar content

Source channel @githubtrending · Post #15364 · Dec 24

#python#ai_tool#darkweb#darkweb_osint#investigation_tool#llm_powered#osint#osint_tool Robin is an AI tool that searches and scrapes the dark web, refines queries with large language models, filters results, and produces a concise investigation summary you can save or export, with Docker and CLI options and support for multiple LLMs (OpenAI, Anthropic, Gemini, local models) to fit your workflow. This helps you save hours of manual searching by automating multi-engine dark-web searches, scraping Onion sites via Tor, filtering noise with AI, and producing ready-to-use reports for faster, more focused OSINT investigations. https://github.com/apurvsinghgautam/robin

Results

4 similar posts found

Search: #gamozone

当前筛选 #gamozone清除筛选
Borkena

@borkena · Post #5998 · 03/13/2026, 05:38 AM

Death Toll from Gamo Zone Flood, Landslide now over 70. Read more. https://borkena.com/2026/03/12/ethiopia-death-toll-from-gamo-zone-flood-landslide-now-over-70/#Ethiopia#News#EthiopianNews#GamoZone#Landslide#flood

Borkena

@borkena · Post #6006 · 03/13/2026, 06:05 PM

የ3 ቀናት ብሔራዊ ሀዘን ታወጀ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተው የመሬት ናዳ እና የጎርፍ አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች የ3 ቀናት ብሔራዊ ሀዘን ታውጇል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፥ በዞኑ ጋጫ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ከጠፉ 125 ሰዎች ውስጥ የ80 ወገኖችን ሕይወት ማለፉን ገልፀዋል። የቀሪ ሰዎች አስከሬን ፍለጋ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ምክር ቤቱ በዜጎቻችን ላይ በተከሰተው አደጋ ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶታል ብለዋል። በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፕብሊክ የሰንደቅ አላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001 አንቀጽ 22 ንዑስ አንቀጽ (2) ብሔራዊ የሀዘን ቀንና ሰንደቅ አላማው ዝቅ ብሎ የሚውለበለብባቸውን ሁኔታዎች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ መደንገጉን ተናግረዋል። በዚሁ መሠረት በመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወታቸው ያለፈው ዜጎቻችንን በማስመልከት ከመጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ቀናት ብሔራዊ የሀዘን ቀን ታውጇል ብለዋል። በእነዚህ ቀናት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰንደቅ አላማ በሁሉም የሀገሪቱ ግዛቶች፣ በኢትዮጵያ መርከቦች፣ በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንጽላ ጽ/ቤት ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ ውሳኔ መተላለፉን ገልፀዋል። #Ethiopia#News#gamozone#ዜና#የጎርፍአደጋ#ጋሞዞን#ቦርከና_ዜና

Borkena

@borkena · Post #5985 · 03/12/2026, 01:56 PM

በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት የሟቾች ቁጥር 107 ደረሰ። ​በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ፣ ካምባ እና ቦንኬ ወረዳዎች በደረሰ የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ የ107 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ​ዋና አስተዳዳሪው በአደጋው 127 ሰዎች መጥፋታቸው እና እስካሁን አለመገኘታቸውን ገልፀዋል። በአካባቢው መልከዓ ምድር አስቸጋሪነት ምክንያት አስክሬን ፍለጋው መጓተቱን ተናግረዋል። ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የዕለት እርዳታ እየቀረበ መሆኑን ጠቁመዋል። ​​#Ethiopia#gamozone#South_Ethiopia#ዜና#ቦርከና_ዜና#ጋሞዞን#የጎርፍአደጋ

Borkena

@borkena · Post #5968 · 03/10/2026, 11:48 AM

እናት ከሁለት ልጆቿ ጋር በመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸው አለፈ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቦንኬ ወረዳ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የአንድ ቤተሰብ የሆኑ እናትና ሁለት ልጆች ሕይወታቸውን አጥተዋል። አባወራው ከፍተኛ ጉዳት ተደርሶባቸው በቦንኬ ጋዜሶ ጤና ጣቢያ ህክምና እየተደረገላቸው ነው ተብሏል። ከአርባ ምንጭ–ጊና–ቦንኬ የሚያገናኘው ዋና መንገድ በመሬት መንሸራተት ተዘግቶ በመገኘቱ ተጎጂውን ወደ ሆስፒታል ለማድረስ ችግር መፍጠሩ ተገልጿል። ዞኑ በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳና በከምባ ዙሪያ ወረዳ አካባቢዎች የጎርፍ ስጋት መኖሩን የጋሞ ዞን ፖሊስ አስጠንቅቋል፤ ነዋሪዎችም ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪውን አቅርቧል። ​ #Ethiopia#Borkena_news#Ethiopiannews#gamozone#አርባምንጭ#ጋሞዞን#ዜና#ቦርከና_ዜና