TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← OnePlus Guide

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Trouver du contenu similaire

Chaîne source @OnePlusGuide · Post #2613 · 24 juin

~ ONEPLUS Z/NORD RITRATTO IN UNA FOTO? ~ #OP#OPZ Ieri OnePlus ha aperto un account Instagram ufficiale chiamato OnePlusLiteZThing che userà per postare teaser e indizi sul nuovo smartphone di gamma medio/alta. Oggi sono state pubblicate alcune foto del nuovo team che sta lavorando in quel settore e a me pare di aver visto qualcosa di sospetto. In una delle foto viene mostrato un telefono su Instagram. Si potrebbe pensare a un banale OnePlus esistente, ma allora perché nasconderne la parte alta? Ricordo che OnePlus Z/Nord dovrebbe essere il primo ad avere il foro in centro. Che ne pensate? Pierre

Hashtags

Résultats

4 posts similaires trouvés

Recherche : #gamozone

当前筛选 #gamozone清除筛选
Borkena

@borkena · Post #6006 · 13/03/2026 18:05

የ3 ቀናት ብሔራዊ ሀዘን ታወጀ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተው የመሬት ናዳ እና የጎርፍ አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች የ3 ቀናት ብሔራዊ ሀዘን ታውጇል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፥ በዞኑ ጋጫ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ከጠፉ 125 ሰዎች ውስጥ የ80 ወገኖችን ሕይወት ማለፉን ገልፀዋል። የቀሪ ሰዎች አስከሬን ፍለጋ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ምክር ቤቱ በዜጎቻችን ላይ በተከሰተው አደጋ ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶታል ብለዋል። በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፕብሊክ የሰንደቅ አላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001 አንቀጽ 22 ንዑስ አንቀጽ (2) ብሔራዊ የሀዘን ቀንና ሰንደቅ አላማው ዝቅ ብሎ የሚውለበለብባቸውን ሁኔታዎች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ መደንገጉን ተናግረዋል። በዚሁ መሠረት በመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወታቸው ያለፈው ዜጎቻችንን በማስመልከት ከመጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ቀናት ብሔራዊ የሀዘን ቀን ታውጇል ብለዋል። በእነዚህ ቀናት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰንደቅ አላማ በሁሉም የሀገሪቱ ግዛቶች፣ በኢትዮጵያ መርከቦች፣ በኢትዮጵያ ኤምባሲዎች እና ቆንጽላ ጽ/ቤት ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ ውሳኔ መተላለፉን ገልፀዋል። #Ethiopia#News#gamozone#ዜና#የጎርፍአደጋ#ጋሞዞን#ቦርከና_ዜና

Borkena

@borkena · Post #5985 · 12/03/2026 13:56

በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት የሟቾች ቁጥር 107 ደረሰ። ​በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ፣ ካምባ እና ቦንኬ ወረዳዎች በደረሰ የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ የ107 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ​ዋና አስተዳዳሪው በአደጋው 127 ሰዎች መጥፋታቸው እና እስካሁን አለመገኘታቸውን ገልፀዋል። በአካባቢው መልከዓ ምድር አስቸጋሪነት ምክንያት አስክሬን ፍለጋው መጓተቱን ተናግረዋል። ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የዕለት እርዳታ እየቀረበ መሆኑን ጠቁመዋል። ​​#Ethiopia#gamozone#South_Ethiopia#ዜና#ቦርከና_ዜና#ጋሞዞን#የጎርፍአደጋ

Borkena

@borkena · Post #5968 · 10/03/2026 11:48

እናት ከሁለት ልጆቿ ጋር በመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸው አለፈ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቦንኬ ወረዳ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የአንድ ቤተሰብ የሆኑ እናትና ሁለት ልጆች ሕይወታቸውን አጥተዋል። አባወራው ከፍተኛ ጉዳት ተደርሶባቸው በቦንኬ ጋዜሶ ጤና ጣቢያ ህክምና እየተደረገላቸው ነው ተብሏል። ከአርባ ምንጭ–ጊና–ቦንኬ የሚያገናኘው ዋና መንገድ በመሬት መንሸራተት ተዘግቶ በመገኘቱ ተጎጂውን ወደ ሆስፒታል ለማድረስ ችግር መፍጠሩ ተገልጿል። ዞኑ በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳና በከምባ ዙሪያ ወረዳ አካባቢዎች የጎርፍ ስጋት መኖሩን የጋሞ ዞን ፖሊስ አስጠንቅቋል፤ ነዋሪዎችም ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪውን አቅርቧል። ​ #Ethiopia#Borkena_news#Ethiopiannews#gamozone#አርባምንጭ#ጋሞዞን#ዜና#ቦርከና_ዜና