TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← Python Заметки

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Најди сличен содржај

Изворен канал @pythonotes · Post #197 · 4 јан.

Подразумеваемые неймспейсы или неявные пакеты. Этот функционал добавлен в Python 3.3 Что он означает? Ранее, до 3.3 пакетами считались лишь директории, в которых есть файл __init__.py. Этот файл одновременно являлся свидетельством того, что директория это Python-пакет, и служил "телом" этого пакета. То есть местом, где можно написать код, как это делается внутри модуля. Этот код исполняется в момент импорта пакета, так что его принято называть "код инициализации пакета". Начиная с версии 3.3 Любая директория считается пакетом и Python будет пытаться использовать любую директорию для импорта. Конечно, не любую в файловой системе, а только те что находятся в sys.path. Это значит, что теперь __init__.py нужно делать только если: 🔸 вам требуется создать код инициализации пакета 🔸 нужна совместимость со старыми версиями Python На мой взгляд это немного упрощает разработку, делает её чище, но с другой стороны убивает некоторую однозначность происходящего. Например, я создал репозиторий со своей библиотекой и рядом положил код примеров или тестов. repo_name/ my_library/ __init__.py main.py examples/ exam1.py exam2.py В этом репозитории пакетом является только my_library, остальные директории это не пакеты, это просто дополнительный код в файлах. Директория examples не добавлена в sys.path, в ней нет рабочих модулей. Но если она лежит рядом с my_library, то Python вполне сможет импортнуть из неё модули, так как посчитает что examples это валидный пакет. Конечно, пример несколько надуманный. Никто не будет добавлять корень репозитория в sys.path. Но, я думаю, суть ясна. Иногда директория это просто директория а не пакет! #basic#pep

Hashtags

Резултати

Пронајдени 8 слични објави

Пребарај: #seaaccess

当前筛选 #seaaccess清除筛选

“ከሁለት፣ ሦስት ዓመት በፊት ለአያሌ መንግሥታት የባሕር ላይ እንቅስቃሴ አደጋ ሊገጥመው ይችላል፤ በዚህ ውስጥ ሚና አልባ ሆነን ከቆየን 130 ሚሊዮን ሕዝብ አደጋ ውስጥ ይወድቃል የሚል አቋም እናነሣ ነበር። በወቅቱ ምንም ነገር ስላልነበረ እምብዛም ተቀባይነት አልነበረውም። አሁን ግን ብዙዎች እያመኑበት ያለ ጉዳይ ነው። ከባህር መራቅ የባህርን ወይም የየብስን ትራንስፖርት ወይም የአየርን ትራንስፖርት ‘ግዴለም፤ በቀላሉ አገኘዋለሁ’ ብሎ ማሰብ የማይቻልበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነው።” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #EBC#Ethiopia#SeaAccess

“ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት ካልሆነች አታድግም ብቻ ሳይሆን ሰፈሩ አይለወጥም፤ ሰፈሩ ሰላም አያገኝም፤ የዓለም ንግድም ይስተጓጎላል።” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #EBC#Ethiopia#PMAbiyAhmed#SeaAccess

የባሕር በር ደኅንነት ጉዳይ ከምንጊዜውም በላይ አንገብጋቢ ሆኗል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ******************* የዓለም የንግድ እና የኢንዱስትሪ ትሥሥር በአየር፣ በየብስ እና በባሕር ሎጂስቲክስ ስጋቶች ውስጥ መውደቁን ተከትሎ የባሕር በር ደኅንነት ጉዳይ ከምንጊዜውም በላይ አንገብጋቢ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ መንግሥት ከዓመታት በፊት የባሕር ላይ እንቅስቃሴ አደጋ ሊገጥመው እንደሚችል በመተንበይ "ከባሕር ከራቅን 130 ሚሊዮን ሕዝብ አደጋ ውስጥ ይወድቃል" የሚል የጸና አቋም ሲያራምድ ቆይቷል። ምንም እንኳን በወቅቱ ለዚህ ጉዳይ በቂ ትኩረት ባይሰጠውም፣ አሁን ላይ ግን ሀገራት የንግድ መስመሮችን ለጥቅማቸውም ሆነ ተቀናቃኞቻቸውን ለመጉዳት ሲሉ በከፍተኛ ደረጃ እየተቆጣጠሩት ይገኛሉ። በመሆኑም ከባሕር መራቅም ሆነ በአንድ መስመር ላይ ብቻ ጥገኛ መሆን አዋጭ ባለመሆኑ፣ ኢትዮጵያ ለዚህ የሎጂስቲክስ አለመረጋጋት አስቀድሞ መተንበይን ‘ፕሮአክቲቭ የሆነ መፍትሔ’ መከተሏን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል። #EBC#Ethiopia#PMAbiyAhmed#SeaAccess

አድማስን ፍለጋ፦ የመላ ኢትዮጵያውያን የጋራ አጀንዳ!! ***************** የባህር በር ለአንድ ሀገር መተንፈሻ ሳንባ ነው። ሳንባው የታፈነ ሰው በሩጫ ተወዳድሮ ሊያሸንፍ እንደማይችል ሁሉ ኢትዮጵያም ዛሬ ዛሬ በየገበያው የምናየው የሸቀጦች ዋጋ መናር፣ የሎጂስቲክስ መጓተትና የኑሮ ውድነት ሰንሰለቱ ሲመረመር መጨረሻው የሚገናኘው ከባህር መራቃችን እና መታነቃችን ጋር ነው። በመሆኑም የባህር በር ፍለጋው የጥቂቶች አጀንዳ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያውያን የፍትህ ጥሪ ነው። በአዶኒያስ ወልደአረጋይ #Ethiopia#SeaAccess#RedSea#EBC https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid07A7EMTS2gbwxuea9kdbkBGNTynJeikQu7h7bLw28KQYk9joN5XN3fVymLgywL9SQl

‎ኢትዮጵያ ወደ ባሕር መመለሷ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው ********************* ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ገዥ፣ የአዱሊስ ወደብ ባለቤትና የገዘፈ የባሕር ኃይል ታሪክ ያላት ሀገር ነበረች። ዛሬ ግን በዓለም ላይ ወደብ ከሌላቸው ሀገራት መካከል በሕዝብ ብዛት ቀዳሚ ሆና መገኘቷ የታሪክ ምጸት ብቻ ሳይሆን፣ የክፍለ ዘመኑ ትልቁ የፖለቲካ ሴራ ውጤት ነው። ለምን ታነቅን? ቢባል ታዲያ መልሱ “በታሪክ አሻጥር ምክንያት” የሚል ነው። የቅኝ ገዥዎች ተንኮል እና በ1983ቱ የሥልጣን ሽግግር ወቅት የታየው የዲፕሎማሲ ዳተኝነት፣ የፖለቲካ ሴራ እና ታሪክ ይቅር የማይለው ስህተት ሀገራችንን በአንድ ጀምበር የባሕር በሯን እንድታጣ አደረጋት። በዚህም ምክንያት በየዓመቱ ለወደብ ኪራይ የምንገብረው 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ እና 95% በጅቡቲ ላይ ጥገኛ መሆናችን፣ የሀገራችንን ዕድገት እና ብሔራዊ ደኅንነት አደጋ ላይ ጥሎታል። ኢትዮጵያ ወደ ባሕር የመመለስ ጥያቄዋ በጉልበት ሳይሆን በታሪክ እና በዓለም አቀፍ የባሕር ሕግ (UNCLOS) መሠረት የመጠቀም መብትን የተመረኮዘ ነው። የቅኝ ግዛት ውሎች እና ያለፉት ትውልዶች ስህተት የ130 ሚሊዮን ሕዝብን የኅልውና መብት ሊቀብሩት አይገባም። ከሴራ ማነቆ ተላቅቆ ወደ ባሕር አድማስ መሻገር፣ ለነገዋ የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚከፈል ትልቁ ዋጋ ነው። "ያለፉት ትውልዶች በውጭ ሴራ እና በራሳቸው ቸልተኝነት የዘጉብንን የባሕር በር፣ ዛሬ በምን ዓይነት ብልሃትና ዲፕሎማሲ እናስመልስ?" ይህ የአሁኑ ትውልዱ ሊመልሰው የሚገባው ታሪካዊ ኃላፊነት ነው። አስተያየት መስጫው ውስጥ ያለው ሊንክ ይህ ሐሳብ በሰፊው የተተነተነበት ጽሑፍ ይዟል፤ እንዲያደነብቡት ጋብዘንዎታል። በአዶኒያስ ወልደአረጋይ #Ethiopia#SeaAccess#RedSea#NoMoreLandLocked

ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ፤ ከሕዳሴ እስከ ባሕር በር! ********************** ዓድዋ ለእኛ ተራራን የመናድ፣ የማይቻለውን የመቻል እና የአንድነት ትልቅ ማህተማችን ነው። ያ ትናንት በዓድዋ ተራራዎች ላይ የነደደው የድል መንፈስ፣ ዛሬም በደምስራችን ውስጥ አለ! ትናንት፦ በዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ፋና ሆንን። ዛሬ፦ ያው የማይበገረው የዓድዋ መንፈስ ታላቁን የሕዳሴ ግድባችንን ዳር አደረሰ። በስንዴ ሉዓላዊነት ታሪክ ተሠራ፤ የዓባይን ወንዝ ለብርሃን እና ለብልፅግና አዋልነው። ነገ፦ ቀጣዩ የታሪክ ምዕራፍ ተጀምሯል፤ የባሕር በር ጉዳይ የሕልውናችን፣ የኢኮኖሚ ነፃነታችን እና የትውልድ ጥያቄ ነው። ትናንት በጋራ ቆመን ያላሸነፍነው ፈተና የለም፤ ዛሬም በዚያው በዓድዋ ፅናት እና በሕዳሴው ወኔ የባሕር በር ጥያቄያችንን በድል እንደምናጠናቅቅ ጥርጥር የለውም! ታሪክ ይደገማል! ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነት ከፍ ብላ ትቀጥላለች! #Ethiopia#AdwaSpirit#GERD#SeaAccess#የሕዳሴግድብ#የባሕርበር#EBC