@ebcnewsnow · Post #51642 · 13.02.2026 г., 16:11
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዕድገት መሠረት እየጣለች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ******* ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2ኛው የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዕድገት መሰረት እየጣለች ነው ብለዋል። 2ኛው የጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ጉባኤው በጣሊያኗ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ እና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተከፍቷል። #EBC#ItalyAfricaSummit
Hashtags