TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← Python Заметки

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Најди сличен содржај

Изворен канал @pythonotes · Post #335 · 29 мар.

В Linux стандартными средствами можно использовать часть оперативной памяти как диск. Для этого требуется указать тип монтирования tmpfs в команде mount mount -t tmpfs -o size=5G tmpfs /mnt/ram Теперь путь /mnt/ram можно использовать как обычный каталог. Для чего это может быть нужно? ▫️ Скорость работы с таким каталогом выше чем многие SSD и тем более HDD. ▫️ Если у вас очень быстрый SSD на NVMe M.2 то такой способ особо не прибавит вам скорости, но поможет сохранить ресурс SSD когда требуется обрабатывать очень много мелких файлов и оперативка позволяет выделить нужный объем. ▫️ Оперативка это энергозависимая память, поэтому выключении питания все файлы безвозвратно теряются. Такой "non persistent" каталог гарантирует удаление временных файлов. Я написал небольшой скрипт для условного теста и сравнения скорости копирования файлов между SSD и RAM. Вот мои результаты: Single File Size: 30.0Gb ssd > ssd: 0:00:12.850 / 2.3Gb/s sdd > ram: 0:00:06.453 / 4.6Gb/s ram > ram: 0:00:06.995 / 4.3Gb/s ram > sdd: 0:00:06.217 / 4.8Gb/s Dir size: 32.7Gb, File count: 11127 ssd > ssd: 0:00:15.063 / 2.2Gb/s sdd > ram: 0:00:08.486 / 3.9Gb/s ram > ram: 0:00:08.032 / 4.1Gb/s ram > sdd: 0:00:07.026 / 4.7Gb/s Скрипт для теста ↗️ На моём железе прирост скорости ~2x. Плюс экономия ресурса SSD. В Windows такой фишки по умолчанию нет, но обязательно найдутся аналогичные решения #linux#triks

Hashtags

Резултати

Пронајдени 7 слични објави

Пребарај: #ausummit2026

当前筛选 #ausummit2026清除筛选

ኢትዮጵያ እንግዶቿን በክብር እየሸኘች ነው **************** በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤና በ2ኛው የጣሊያን-አፍሪካ ስብሰባ ላይ የተሳተፉ መሪዎች በኢትዮጵያ የነበራቸውን ቆይታ በስኬት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ወደ አገራቸው መመለስ ጀምረዋል። መሪዎቹ ከቦሌ ዓለም-አቀፍ አየር ማረፊያ ሲነሱም የክብር አሸኛኘት እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#ebcdotstream#Ethiopia#AUSummit2026

ለ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ከእንግዶች አቀባበል ጋር በተያያዘ ዝግ የሚደረጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ ******************** የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል 39ኛውን የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ አስመልክቶ አጠቃላይ የጸጥታ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወቅ ሲሆን የተሽከርካሪ ፍሰቱን ለማሳለጥና ከእንግዶች አቀባበል ጋር በተያያዘ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። በዚህም ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ብራስ እንዲሁም ከቦሌ መድኃኒያለም በአትላስ ወደ ቅዱስ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ በመሪዎቹ ጉባኤ ምክንያት ከዛሬ የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረግ ይሆናል። በተጨማሪም በሌሎች እንግዶች በሚያርፉባቸው ዋና ዋና አደባባዮችና የአጀብ መስመሮች አሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠትና የትራፊክ ፖሊስ አባላትን ትዕዛዝ በማክበር የተለመደ ቀና ትብብራቸውን እንዲያደርጉ፤ በተጠቀሱት ቦታዎች ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪዎችን ማቆም የተከለከለ መሆኑንም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙም በነጻ የስልክ መስመሮች 990፣ 991፣ 987፣ 816 እንዲሁም በ011-1-26-43-59፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (Citizen Engagement Application) EFPApp በመጠቀም ጥቆማ መስጠት እንደሚገባም ጥሪ ተላልፏል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#AUSummit2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ጋር ተወያዩ ******* አዲሱን የኅብረታችን ሊቀመንበር፤ የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬን አግኝቼ በተረከቡት ኃላፊነት ደስታዬን ገልጬላቸዋለሁ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የአፍሪካውያን ጠንካራ ትብብር እና ቀጣናዊ ግንኙነቶችን ለማሳደግ በሚያስችሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገናል ብለዋል። #EBC#PMAbiy#Ethiopia#AUSummit2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቦትስዋና ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮን ጋር ተወያዩ ****************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቦትስዋና ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ የቦትስዋና ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮን አግኝቼ፤ በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች፣ ለተሻለ ኢኮኖሚያዊ ትብብር ያሉ እድሎች እና አፍሪካን ቀጣይ የሚመራ ትውልድን ማብቃት ላይ በጋራ በምንሰራበት አውድ ዙሪያ ውይይት አድርገናል ብለዋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#PMAbiy#Diplomacy#AUSummit2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ፕሬዝዳንታዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር መሃመድ አልመንፊ ጋር ተወያዩ ***************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ፕሬዝዳንታዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር መሃመድ አልመንፊ ጋር በቀጣናዊ ልማት እና የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#PMAbiy#Diplomacy#AUSummit2026

የተመድ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አዲስ አበባ ገቡ **************** የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በ39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል። ዋና ጸሀፊው ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የፕላንና ልማት ሚኒስተር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል። 39ኛው የኅብረቱ የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፥ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ ይካሄዳል። በጉባኤው የሚሳተፉ መሪዎችም ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ በመግባት ላይ ናቸው። በሞላ አለማየሁ #EthiopianBroadcastingCorporation#Ethiopia#UNSG#AntónioGuterres#AUSummit2026

ከጉባኤ አዳራሾች ባሻገር የሚተርክ አዲስ ገጽታ እና የኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊ ዝግጁነት ******************* ኢትዮጵያ 39ኛውን የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 2ኛውን የጣሊያን-አፍሪካ ስብሰባ ለመካፈል ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ከፍተኛ ልዑካንን ለመቀበል ከመቼውም ጊዜ በላይ ስንዱ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። መዲናዋ በከፍተኛ ጥራትና በዘመናዊ መልክ የተገነቡ ዓለም አቀፍ የስብሰባ አዳራሾችን እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ ምቹ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማሟላት እንግዶቿን ለመቀበል በላቀ ደረጃ መዘጋጀቷን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። ይህ አዲሱና ማራኪው የከተማዋ ገጽታ የእንግዶችን ቆይታ ልዩና የማይረሳ እንደሚያደርገው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተሳታፊዎች ከጉባኤው መድረኮች ባሻገር በአፍሪካውያን ጥረት እያደገ የመጣውን አዲሱን የቱሪዝም ዘርፍ እንዲመለከቱና ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ይህ ዝግጁነት ኢትዮጵያ ለዲፕሎማሲያዊ ሁነቶች ያላትን ምቹነት የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን፣ አህጉራዊ ትብብርንና የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ያረጋገጠ መሆኑ ተመላክቷል። #Ethiopia#PMAbiyAhmed#AfricanUnion#AUSummit2026#ItalyAfricaSummit#TourismEthiopia#EthiopianBroadcastingCorporation