TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← Python Заметки

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Најди сличен содржај

Изворен канал @pythonotes · Post #403 · 31 дек.

С Новым Годом!🎄☃️❄️ Снова этот рубеж подведения итогов и определения планов на следующее 365 дней. Что же мы успели застать в 2к25? 🔸 AI снова делает скачёк в развитии, как по качеству, так и по затратам на ресурсы Продолжая расшатывать все рынки 🔸 Эпичный прорыв цен на железо (из-за первого факта). Сначала оперативка, потом и остальные подтянулись. Успели закупиться вовремя? 🔸 Новый виток "борьбы с интернетом" в РФ Работать всё сложней 🔸 Опенсорсный проект MinIO закрылся Теперь только в облаке и только за денежку Но не всё так плохо! 🔸 Всё больше уверенных мнений, что AI нас не заменит Но всем нужно адаптироваться к новым реалиям и инструментам 🔸 uv ворвался в прод Так и стандартом станет скоро 🔸 Вышел Django 6 Достаточно ли изменений для мажорной версии? 🔸 Вышел PIthon 3.14 с NO-GIL режимом Раньше это считалось невозможным! 🔸 В том же 3.14 мы получили полноценные Субинтерпретаторы и JIT И другие оптимизации 🔸 Язык Rust теперь официально второй язык ядра Linux Хоть и не без проблем 🔸 Проекту pythonotes 6 лет 🎂 Скоро в школу) Мир вокруг меняется постоянно и всё с большей скоростью. Не ищите виновных, просто адаптируйтесь и постоянно учитесь. И всё будет пучком! 😎 Оглядываясь назад в прошлое, задумайтесь, можете ли вы сказать тому себе из прошлого СПАСИБО за то, что вы имеете в настоящем? И хорошенько подумайте в этом настоящем, что нужно делать уже сейчас, чтобы вы из будущего стали лучшей версией себя настоящего и гордились своей версией из прошлого за заботу о будущем. Sir Christopher Edward Nolan :) #offtop

Hashtags

Резултати

Пронајдени 7 слични објави

Пребарај: #ausummit2026

当前筛选 #ausummit2026清除筛选

ኢትዮጵያ እንግዶቿን በክብር እየሸኘች ነው **************** በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤና በ2ኛው የጣሊያን-አፍሪካ ስብሰባ ላይ የተሳተፉ መሪዎች በኢትዮጵያ የነበራቸውን ቆይታ በስኬት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ወደ አገራቸው መመለስ ጀምረዋል። መሪዎቹ ከቦሌ ዓለም-አቀፍ አየር ማረፊያ ሲነሱም የክብር አሸኛኘት እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#ebcdotstream#Ethiopia#AUSummit2026

ለ39ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ከእንግዶች አቀባበል ጋር በተያያዘ ዝግ የሚደረጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ ******************** የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል 39ኛውን የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ አስመልክቶ አጠቃላይ የጸጥታ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወቅ ሲሆን የተሽከርካሪ ፍሰቱን ለማሳለጥና ከእንግዶች አቀባበል ጋር በተያያዘ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። በዚህም ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ብራስ እንዲሁም ከቦሌ መድኃኒያለም በአትላስ ወደ ቅዱስ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ በመሪዎቹ ጉባኤ ምክንያት ከዛሬ የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረግ ይሆናል። በተጨማሪም በሌሎች እንግዶች በሚያርፉባቸው ዋና ዋና አደባባዮችና የአጀብ መስመሮች አሽከርካሪዎች ቅድሚያ በመስጠትና የትራፊክ ፖሊስ አባላትን ትዕዛዝ በማክበር የተለመደ ቀና ትብብራቸውን እንዲያደርጉ፤ በተጠቀሱት ቦታዎች ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪዎችን ማቆም የተከለከለ መሆኑንም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙም በነጻ የስልክ መስመሮች 990፣ 991፣ 987፣ 816 እንዲሁም በ011-1-26-43-59፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (Citizen Engagement Application) EFPApp በመጠቀም ጥቆማ መስጠት እንደሚገባም ጥሪ ተላልፏል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#AUSummit2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ጋር ተወያዩ ******* አዲሱን የኅብረታችን ሊቀመንበር፤ የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት ኢቫሪስቴ ንዳይሺሚዬን አግኝቼ በተረከቡት ኃላፊነት ደስታዬን ገልጬላቸዋለሁ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። የአፍሪካውያን ጠንካራ ትብብር እና ቀጣናዊ ግንኙነቶችን ለማሳደግ በሚያስችሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገናል ብለዋል። #EBC#PMAbiy#Ethiopia#AUSummit2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቦትስዋና ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮን ጋር ተወያዩ ****************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቦትስዋና ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ የቦትስዋና ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮን አግኝቼ፤ በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች፣ ለተሻለ ኢኮኖሚያዊ ትብብር ያሉ እድሎች እና አፍሪካን ቀጣይ የሚመራ ትውልድን ማብቃት ላይ በጋራ በምንሰራበት አውድ ዙሪያ ውይይት አድርገናል ብለዋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#PMAbiy#Diplomacy#AUSummit2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ፕሬዝዳንታዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር መሃመድ አልመንፊ ጋር ተወያዩ ***************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ፕሬዝዳንታዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር መሃመድ አልመንፊ ጋር በቀጣናዊ ልማት እና የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#PMAbiy#Diplomacy#AUSummit2026

የተመድ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አዲስ አበባ ገቡ **************** የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በ39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል። ዋና ጸሀፊው ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የፕላንና ልማት ሚኒስተር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል። 39ኛው የኅብረቱ የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፥ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ ይካሄዳል። በጉባኤው የሚሳተፉ መሪዎችም ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ በመግባት ላይ ናቸው። በሞላ አለማየሁ #EthiopianBroadcastingCorporation#Ethiopia#UNSG#AntónioGuterres#AUSummit2026

ከጉባኤ አዳራሾች ባሻገር የሚተርክ አዲስ ገጽታ እና የኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊ ዝግጁነት ******************* ኢትዮጵያ 39ኛውን የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 2ኛውን የጣሊያን-አፍሪካ ስብሰባ ለመካፈል ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ከፍተኛ ልዑካንን ለመቀበል ከመቼውም ጊዜ በላይ ስንዱ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። መዲናዋ በከፍተኛ ጥራትና በዘመናዊ መልክ የተገነቡ ዓለም አቀፍ የስብሰባ አዳራሾችን እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ ምቹ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማሟላት እንግዶቿን ለመቀበል በላቀ ደረጃ መዘጋጀቷን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። ይህ አዲሱና ማራኪው የከተማዋ ገጽታ የእንግዶችን ቆይታ ልዩና የማይረሳ እንደሚያደርገው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተሳታፊዎች ከጉባኤው መድረኮች ባሻገር በአፍሪካውያን ጥረት እያደገ የመጣውን አዲሱን የቱሪዝም ዘርፍ እንዲመለከቱና ቆይታቸውን እንዲያራዝሙ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ይህ ዝግጁነት ኢትዮጵያ ለዲፕሎማሲያዊ ሁነቶች ያላትን ምቹነት የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን፣ አህጉራዊ ትብብርንና የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ያረጋገጠ መሆኑ ተመላክቷል። #Ethiopia#PMAbiyAhmed#AfricanUnion#AUSummit2026#ItalyAfricaSummit#TourismEthiopia#EthiopianBroadcastingCorporation