@ebcnewsnow · Post #53271 · 10.04.2026 г., 10:17
የስቅለት በዓል በወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ እየተከበረ ነው ************** የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በአምስት ኪሎ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች እየተከበረ ይገኛል። በመርሐ ግብሩ ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ድነት ሲል በመስቀል ላይ የከፈለው መከራና መስዋዕትነት በስፋት ተነስቷል። ይህ በመስቀል ላይ የተፈጸመው ተግባር ሰውን ከኃጢአት ባርነት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ፣ የዛሬው ትውልድም ከጥላቻና ከቂም በቀል ባርነት ነጻ መውጣት እንዳለበት ተገልጿል። የመስቀሉ ፍቅር የክፋት ሁሉ ማክተሚያ፣ የይቅርታና የትሕትና ትምህርት መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፤ አማኙም ይህን ታላቅ መሠረት በመከተል ባለፈ ታሪክ ላይ ከመቆዘም ይልቅ ለነገው ብሩህ ተስፋ ይቅርታን ስንቅ ሊያደርግ እንደሚገባ መልዕክት ተላልፏል። በቤተ ክርስቲያኒቱ በተዘጋጀው በዚህ አገልግሎት ላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች፣ አገልጋዮች፣ ምዕመናን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል። በዕድሉ ፈቀደ #EthiopianBroadcastingCorporation#Ethiopia#GoodFriday#MekaneYesus#AddisAbaba