TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← Python Заметки

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Најди сличен содржај

Изворен канал @pythonotes · Post #65 · 8 апр.

Небольшой трик с регулярными выражениями который редко вижу в чужом коде. Допустим, вам нужно распарсить простой текст и вытащить оттуда пары имя+телефон. Вернуть всё это надо в виде списка словарей. Возьмем очень простой пример текста. >>> text = ''' >>> Alex:8999123456 >>> Mike:+799987654 >>> Oleg:+344456789 >>> ''' Соответственно, для выделения нужных элементов будем использовать группы. Получится такой паттерн: (\w+):([\d+]+) Как мы будем формировать словарь из найденных групп? >>> import re >>> results = [] >>> for match in re.finditer(r"(\w+):([\d+]+)", text): >>> results.append({ >>> "name": match.group(1), >>> "phone": match.group(2) >>> }) >>> print(results) [{'name': 'Alex', 'phone': '8999123456'}, ...] Можно немного сократить запись используя zip >>> results = [] >>> for match in re.finditer(r"(\w+):([\d+]+)", text): >>> results.append(dict(zip(['name', 'phone'], match.groups()))) Но есть способ лучше! Это именованные группы в regex. Можно в паттерне указать имя группы и результат сразу забрать в виде словаря. >>> for match in re.finditer(r"(?P<name>\w+):(?P<phone>[\d+]+)", text): >>> results.append(match.groupdict()) То есть всё что я сделал, это добавил в начале группы (внутри сбокочек) такую запись: (?P<group-name>...) Теперь найденная группа имеет имя и можно обратиться к ней как к элементу списка >>> name = match['name'] Либо забрать сразу весь словарь методом groupdict() >>> match.groupdict() #tricks#regex

Резултати

Пронајдени 5 слични објави

Пребарај: #election2018

当前筛选 #election2018清除筛选

ምርጫ - የነገን ብሩህ ተስፋ ለመቅረጽ የሚያስችል ቁልፍ መሣሪያ ****** ታላቁ የሰላም ተምሳሌት ኔልሰን ማንዴላ "ምርጫ የተሻለች ዓለምን ለመገንባት በእጃችን ያለ ታላቅ ዕድል ነው" የሚል አባባል ነበራቸው። ይህም የምርጫ ድምፃችን ከማንኛውም ቁሳዊ ኃይል ይልቅ የነገን ብሩህ ተስፋ ለመቅረጽ በእጃችን ያለ ዋነኛ ቁልፍ መሣሪያ መሆኑን ያሳያል። መራጭ መሆን መብት ብቻ ሳይሆን ለሀገርና ለሚመጣው ትውልድ የሚደረግ ታላቅ የዜግነት ኃላፊነት ነው። በምንሰጠው ድምፅ ፍትሕን፣ ልማትንና ሰላምን የመገንባት አቅም አለን። የምርጫ ድምፃችን የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሠረት ነው። ስለዚህ ታሪክን የዴሞክራሲ ታሪክን በጎ መልኩ ለመገንባት እያንዳንዱ ድምፅ የራሱ የሆነ ክቡር ዋጋ እንዳለው ተገንዝበን፣ በበሰለና በኃላፊነት ስሜት መሳተፍ ይገባል። ምርጫ የግለሰቦች ውድድር ሳይሆን የጋራ ቤታችንን የምናድስበት የጋራ ራዕያችን ነው! እኔ የምርጫ ጉዳይ ያገባኛል፣ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እሳተፋለሁ! እርስዎስ? በጌትነት ተስፋማርያም #EBC#Election2018#Ethiopia

ወደ ለምለሙ ምድር ለመሻገር የሁላችንም እጅ ያስፈልጋል ************** ጥንት በአንድ ታላቅ ተራራ ግርጌ የሚኖሩ ሰዎች ወደ ማዶ የሚገኘው ለም ምድር ለመሻገር ፈልገዋል። ሆኖም ወደዚያ ለመሻገር የሚያስችል ድልድይ አልነበረም። የሀገሬው ሽማግሌዎችም አንድ ጥበብ ተናገሩ፤ "ጠንካራ ድልድይ መሥራት ይገባል፤ ይህ ድልድይ የሚገነባው እያንዳንዱ ሰው በሚያመጣው ጠጠር ነው" አሉ። እያንዳንዷ እናት፣ እያንዳንዱ ወጣትና አዛውንት አንዲት ጠጠር አመጡ። አንዱ "ጠጠሬ ትንሽ ናት" ብሎ አላቃለለም፤ ሌላውም "እኔ ባላመጣ ምን ይጎድላል?" ብሎ ወደ ኋላ አላለም። በመጨረሻም፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ትናንሽ ጠጠሮች ተከመሩ። እነዚያ ተለይተው ሲታዩ የማይረቡ የሚመስሉ ትናንሽ ጠጠሮች ተገጣጥመው ታላቅና ጽኑ ድልድይ ገነቡ። ሕዝቡም በገዛ እጁ በገነባው ድልድይ ላይ ተራምዶ ወደ ለምለሙ ምድር ተሻገረ። ያ ድልድይ የቆመው በአንድ ሰው ጥንካሬ ሳይሆን፣ በእያንዳንዱ ግለሰብ ተሳትፎና እምነት ነበር። ምርጫ ልክ እንደዚያ ድልድይ ግንባታ ነው። እያንዳንዷ ድምፅ እንደ አንዲት ጠጠር ናት። ጠጠሮቹ ሲደመሩና ሲተባበሩ ማንም የማይበግረው መሠረት ይሆናሉ። የዴሞክራሲው ድልድይ እንዲጸና፣ የነገው ብርሃን እንዲመጣና ለምለሙ ተራራ እንዲደረስበት፤ እጅ ለእጅ ተያይዘን በምርጫ መሳተፍ የዜግነት ግዴታችን ብቻ ሳይሆን የታሪክ አደራችንም ነው። #EBC#election2018#Ethiopia#EthiopianBroadcastingCorporation

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ አሃዞች *********** ከየካቲት 28 - መጋቢት 10/2018 ዓ.ም ጠቅላላ የተመዘገቡ መራጮች፦ ከ18.5 ሚሊዮን በላይ የጾታ ስብጥር፦ ወንዶች፦ 10,133,639 ሴቶች፦ 8,422,698 የምርጫ አስፈጻሚዎች ብዛት፦ 187,028 ባለሙያዎች #Ethiopia#Election2018#Democracy#EthiopianBroadcastingCorporation

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የእጩዎች ዝርዝር ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ይፋ ይደረጋል - ምርጫ ቦርድ ********************* የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደሩ እጩዎች ዝርዝር ከዛሬ ምሽት ጀምሮ በየምርጫ ክልሎቹ ይፋ እንደሚደረግ አስታውቋል። የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንደገለጹት፤ ቦርዱ በፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡለትን የእጩዎች ዝርዝርና ተያያዥ ሰነዶችን በጥንቃቄ የመመርመር ሥራውን አጠናቋል። በዚህ የምርጫ ሒደት 47 ፖለቲካ ፓርቲዎች የሚሳተፉ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 10 ሺህ 934 እጩዎች ለምርጫ ቀርበዋል። ከእነዚህም መካከል 2 ሺህ 198 እጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ 8 ሺህ 736 እጩዎች ደግሞ ለክልል ምክር ቤቶች የሚወዳደሩ ናቸው። በምዝገባው ሂደት 73 የግል እጩዎች የተካተቱ ሲሆን፣ ከጠቅላላው የእጩዎች ቁጥር ውስጥ 2 ሺህ 760 ሴቶችና 8 ሺህ 174 ወንዶች መሆናቸውን ቦርዱ ገልጿል። በሳምሶን ገድሉ #EBC#Ethiopia#Election2018#NEBE#Democracy#Candidates#ኢትዮጵያ#ምርጫ2018

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ የሚከናወንባቸው ሦስት ዘመናዊ አማራጮች ***************** ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚከናወነው የመራጮች ምዝገባ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ባገናዘበ መልኩ በሦስት ዋና ዋና አማራጮች እንደሚከናወን ቦርዱ አስታውቋል። የመጀመሪያው አማራጭ መራጮች በተለመደው አሠራር በአካል በምርጫ ጣቢያ በመገኘት ምዝገባ የሚያከናውኑበት መደበኛ ሂደት ነው። ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምዝገባ ሂደቱን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግ 'ምርጫዬ' የተሰኘ አዲስ የሞባይል መተግበሪያ በቅርቡ ተደራሽ ያደርጋል። መራጮች ይህንን መተግበሪያ ከፕሌይ ስቶር (Play Store) ወይም ከአፕ ስቶር (App Store) በማውረድ ባሉበት ሆነው ራሳቸውን መመዝገብ የሚችሉ ሲሆን፥ ለዚሁ አገልግሎት የተዘጋጀውን የዌብ አማራጭ ሊንክም በቦርዱ ድረ-ገጽ ላይ ማግኘት ይቻላል። ሦስተኛው አማራጭ ደግሞ በምርጫ ጣቢያዎች በሚገኙ የምርጫ አስፈጻሚዎች እገዛ በታብሌት (Tablet) የሚከናወን የዲጂታል ምዝገባ ሂደት መሆኑ ተገልጿል። በምርጫ ጣቢያም ሆነ በግል ስልክ የሚከናወኑት የዲጂታል ምዝገባ አማራጮች ተፈጻሚ የሚሆኑት ቦርዱ የኢንተርኔት ተደራሽነትን መሠረት በማድረግ ይፋ በሚያደርጋቸው የተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ብቻ መሆኑ ታውቋል። በቦርዱ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል። #Ethiopia#Election2018#DigitalRegistration#NEBE#EthiopianElection#NewsUpdate