TGTGInsightаналитика telegramLIVE / telegram public index
← Фотогалерея Валерия Плотникова

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

Найти похожее

Источник @vfplotnikov · Post #1663 · 29 апр.

Актриса ЛАРИСА УДОВИЧЕНКО родилась 29 апреля 1955 года в Вене (Австрия). Подробнее: https://zen.yandex.ru/media/id/5e0e2740028d6800ad2e198e/glazami-fotografa-plotnikova-larisa-udovichenko-rodilas-29-aprelia-6054449b53791e021b279558 #Удовиченко#29апреля#Плотников

Результаты

Найдено 2 похожих постов

Поиск: #irancrisis

当前筛选 #irancrisis清除筛选
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)

@ebcnewsnow · Post #53143 · 07.04.2026, 15:32

ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለኢራን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጡ፤ ኢራን ዜጎቿ የኃይል መሠረተ ልማትን እንዲጠብቁ ጠይቃለች ************************* የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ‘ትሩዝ ሶሺያል’ በተሰኘው የማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ኢራን ከአሜሪካ ጋር በአስቸኳይ ስምምነት ላይ ካልደረሰች "መላው ሥልጣኔዋ ዛሬ ምሽት ይጠፋል፤ ዳግመኛም ተመልሶ አይመጣም" ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ፕሬዚዳንቱ ይህ እንዲሆን እንደማይፈልጉ ቢገልጹም፣ የተሰጠው የሰዓታት ቀነ-ገደብ እየተጠናቀቀ በመሆኑ "ሳይሆን አይቀርም" በማለት ክስተቱ የማይቀር መሆኑን አመልክተዋል። ኢራን ስትራቴጂካዊውን የሆርሙዝ ወሽመጥ በመዝጋት የዓለምን ኢኮኖሚ "አግቻለሁ" በማለት የምታደርገውን ሙከራ እንደ ትልቅ ስህተት እና የአስገዳጅነት ስልት የቆጠሩት ትራምፕ፣ ለ47 ዓመታት የዘለቀው ማስፈራራት፣ ሙስና እና ሞት ዛሬ ምሽት ያበቃል ብለዋል። አክለውም በዓለም ረጅም ታሪክ ውስጥ እጅግ ወሳኝ የሆነው ውጤት ዛሬ ምሽት እንደሚታወቅ እና ምናልባትም "አስደናቂ አብዮታዊ ለውጥ" ሊመጣ እንደሚችል ጠቁመዋል። ኢራን በመካከለኛ ወገኖች በኩል የቀረበላትን የጊዜያዊ ተኩስ አቁም የሰላም ዕቅድ ውድቅ ማድረጓን የገለጸች ሲሆን፣ ዘላቂ ድርድር ሊጀመር የሚችለው አሜሪካ እና እስራኤል ጥቃታቸውን አቁመው ለደረሰው ጉዳት ካሳ ሲከፍሉ ብቻ መሆኑን አስታውቃለች። በተጨማሪም ማንኛውም የወደፊት ስምምነት የሆርሙዝ ወሽመጥ በኢራን ቁጥጥር ሥር ሆኖ በሚያልፉ መርከቦች ላይ ቀረጥ የመጣል መብቷን ሊያከብር እንደሚገባ የሀገሪቱ ከፍተኛ ምንጮች አመልክተዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል። #Trump#IranCrisis#HormuzStrait#BreakingNews#MiddleEastConflict