@ebcnewsnow · Post #51692 · 2026/02/15 08:16
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኮትዲቯር ምክትል ፕሬዝዳንት ቲዬሞኮ ሜይሊየት ኮኔን ጋር ተወያዩ ******* ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኮትዲቯር ምክትል ፕሬዝዳንት ቲዬሞኮ ሜይሊየት ኮኔን ጋር መወያየታቸውን አስታወቁ። መሪዎቹ በዛሬው ዕለት ባካሄዱት ውይይት፣ በአኅጉራዊ እና የሁለቱ ሀገራት የወል ፍላጎቶች በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ይህ የሁለቱ መሪዎች ውይይት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ከሚገኘው 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ጎን ለጎን የተከናወነ መሆኑ ታውቋል። #PMAbiy#Ethiopia#EBC#cotedivoire
Hashtags