@ebcnewsnow · Post #52296 · 2026/03/11 16:13
የሆርሙዝ መዘጋት እና የነዳጅ ዋጋ መናር በዓለም ኢኮኖሚ ላይ የደቀነው ስጋት ****************** በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥምረት በኢራን ላይ የተሰነዘረውን ጥቃት ተከትሎ በመካከለኛው ምሥራቅ በተከሰተው ጦርነት የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ በመዘጋቱ፣ ዓለም አቀፉ የነዳጅ ገበያና ኢኮኖሚ ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ወድቋል። ይህንኑ ተከትሎ ከ85 በላይ ሀገራት የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አድርገዋል። በአሜሪካ የ20 በመቶ ጭማሪ ሲታይ፣ በእስያ ሀገራት (እንደ ቬየትናም እና ላኦስ) ከ33 እስከ 50 በመቶ የሚደርስ አስከፊ የዋጋ ንረት ተመዝግቧል። ጃፓን እና ፈረንሳይ የስትራቴጂክ የነዳጅ ክምችታቸውን ለመልቀቅ ተገድደዋል። ደቡብ ኮሪያ ከ30 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የነዳጅ ዋጋ የጣሪያ ገደብ አውጥታለች። የቡድን ሰባት ሀገራት የፋይናንስ ሚኒስትሮች የአቅርቦት እጥረቱን ለመታደግ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠዋል። እንደ ፓኪስታን እና ባንግላዴሽ ያሉ ሀገራት ፍጆታን ለመቀነስ ትምህርት ቤቶችን እስከመዝጋት ደርሰዋል። ቀውሱ ከነዳጅ አልፎ በምግብ ዋስትና፣ በማዳበሪያ አቅርቦት እና በኢንዱስትሪ ምርቶች (ፕላስቲክ እና ጨርቃጨርቅ) ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጫና ፈጥሯል። የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ሁኔታው ወደ ‘ስታግፍሌሽን’ (የዋጋ ንረትና የኢኮኖሚ መቀዝቀዝ ጥምረት) ሊያመራ እንደሚችል እና ዓለም አቀፍ የኑሮ ቀውስ ሊያስከትል እንደሚችል እያሰገነዘቡ ነው። በለሚ ታደሰ ሙሉ መረጃውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ #FuelCrisis#GlobalEconomy#EnergySecurity#IranWarImpact#OilPrices2026#G7Summit