EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
@ebcnewsnow · Post #54008 · 2026/04/25 10:39
ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር ማያርድት ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመለሱ ************** በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሲያደርጉ የቆዩት የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር ማያርድት ጉብኝታቸውን አጠናቀው ዛሬ ተመልሰዋል። ፕሬዝዳንቱ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ሲመለሱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት ሽኝት አድርገውላቸዋል። ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኬር በቆይታቸው ከከፍተኛ የኢትዮጵያ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸው ይታወሳል። በአሸናፊ እንዳለ #EthiopianBroadcastingCorporation#ሳልቫ_ኬር#ተመስገን_ጥሩነህ#Ethiopia#SouthSudan#SalvaKiir#Diplomacy