EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
@ebcnewsnow · Post #51624 · 2026/02/12 19:46
የተመድ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አዲስ አበባ ገቡ **************** የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በ39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል። ዋና ጸሀፊው ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የፕላንና ልማት ሚኒስተር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል። 39ኛው የኅብረቱ የመሪዎች ጉባዔ "ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፥ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ ይካሄዳል። በጉባኤው የሚሳተፉ መሪዎችም ወደ አፍሪካ መዲና አዲስ አበባ በመግባት ላይ ናቸው። በሞላ አለማየሁ #EthiopianBroadcastingCorporation#Ethiopia#UNSG#AntónioGuterres#AUSummit2026