@ebcnewsnow · Post #53351 · 2026/04/11 13:50
የመራጮች ምዝገባ ዜጎች ከሀገረ መንግሥቱ ጋር የሚገቡት "የዜግነት ውል" ነው ******************** የመራጭነት ካርድ መያዝ ማለት በሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ ተመልካች ከመሆን ወጥቶ ውሳኔ ሰጪ መሆን ነው። የነገዋ ኢትዮጵያ ሥዕል የሚሣለው ዛሬ እርስዎ በሚወስዱት ካርድ አማካኝነት ነው። ዛሬ የምምናወጣው ካርድ ነገ ለምንጠይቅበት መብት፣ ለምንሻው ተጠያቂነት እና ለምንመኘው ሉዓላዊነት ብቸኛው ሕጋዊ እና ሰላማዊ መሣሪያችን ነው። የመመዝገብ ጥልቅ ትርጉም፦ • የሀገረ መንግሥት ፅናት፦ አንድ ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚቆመው በሕዝብ ፈቃድ ላይ ነው። መመዝገብ ማለት "ሀገሬ በእኔ ድምፅ ትመራለች" የሚል ፅኑ እምነትን በተግባር ማሳየት ነው። • የፖለቲካ ተሳትፎ ጥራት፦ ዴሞክራሲ በምኞት አይገነባም፤ በሂደት እንጂ። ካርድ ማውጣት በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ወሳኝ ተዋናይ የመሆን ፍላጎትን እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ያለንን ዝግጁነት የሚለካ ብሔራዊ ሚዛን ነው። Ethiopian Broadcasting Corporation #EBC#Ethiopia#elections#voterscard