TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← #HaSab
#HaSab avatar

TGINSIGHT POST

Post #7

@Hasab_2016

#HaSab

ዕይታዎች230የዕይታ ቁጥር
ታትሟልሴፕቴ 1010/09/2023 08:16 ከሰዓት
ይዘት

የልጥፍ ይዘት

#HaSab #Fishery የምስራቅ አፍሪካ የወሃ ማማ ላይ አሳ እንደልብ አይበላም! እጅግ አሳዛኝ እውነት ነው።ሀገራችን ኢትዮጵያ 13,637 sqkm የሚሆነው ምድሯ በወሃ ተሸፍኖ 51 ሺ ቶን በላይ አሳ በአመት የማምረት አቅም እያላት የምታመርታው እዚህ ግባ የማይባል ነው። በከተሞች አሳ መብላት የቅንጦት ነገር ነው፣ ሀይቅ አልያም ጥልልቅ ወንዞች በሌለባቸው አከባቢዎች አሳ ከመአድ ዝርዝር ውስጥ የለም። እንዲህም ሆኖ ከተጠመደ በኋላ በሚያጋትም ብክነት፣ የመሠረተ ልማት ያለመሟላት እና ትራንስፖርት ችግር ፣የአየር ንብረት ለውጥ እና ሌሎች ችግሮች ምክንያት ጠግበን ያላጣጣምነውን የአሳ ሀብት እያጣን ነው። እየተመናመነ ራሳቸውን ያልተኩ ትንንሽ አሶች እየተጠመዱ ቀጣይነት ያለው ሀብት እንዳይኖረን እየሆንን ነው። ከዚህ በፊት የታቀዱም የተሞከሩም የአሳ ሀብታችንን እንድንጠቀም የሚያደርጉ ስራዎች ሊበረታቱ ይገባል፣ በአሳ ዝርያዎቻችን የሀብት መጠናችን እና የአመጋገብ ስርዓታችን ጥናቶች በበቂ መንገድ ቢደረጉ ቀላል ፋይዳ አይኖረውም። የፈጠራ ስራዎች ተስፋፍተው በዘርፉ ቢሰማሩ አስቡት! አምራቾች ድፈሩ! Aquaculture ሀገራችን ውስጥ መስፋፋት አለበት። ሰዎች ከሀይቅ እና ወንዞቻችን በተጨማሪ በሰውሰራሽ ገንዶዎች አሳን ማምረት እና ማከፋፈል ይችላሉ። የሚችለውም የሚመለከተውም በተቀናጀ ሁኔታ ከሰራ በምስራቅ አፍሪካ የወሃ ማማ አሳ እንደልብ ይበላል። Yared E. (3rd year DVM student at AAU-CVMA)