@ebcnewsnow · Post #51411 · 01.02.2026 г., 10:43
📍 "የነገዋ አፍሪካ ብርሃን፦" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተርፍ የንጹህ ኃይል መሠረት መጣሉን ተናገሩ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛ አጋማሽ የ"አፍሪካ ዘመን" እንዲሆን ዛሬውኑ ጠንካራ መሠረት መጣል እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሳሰቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፍሪካን ወደ ላቀ ዕድገት የሚያሻግሩ ሁለት ቁልፍ ምሰሶዎችን ጠቁመዋል፦ 🔹 ብቁ ትውልድ መገንባት፦ በሕፃናት ትምህርት ላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ነገን የሚረከብ ብቁ ዜጋ ማዘጋጀት። 🔹 ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ ልማት፦ አካባቢን የማይበክልና ለቀጣይ ትውልድ የሚተርፍ የአረንጓዴ መሰረተ ልማት ግንባታን ማፋጠን። ቁልፍ ነጥቦች፦ ✅ የንጹህ ኃይል ስጦታ፦ ኢትዮጵያ ለቀጣዩ የአፍሪካ ዕድገት የምታበረክተው ትልቁ ስጦታ ከውኃ፣ ከንፋስና ከጂኦተርማል የሚመነጭ ታዳሽ ኃይል መሆኑ ተገልጿል። ✅ የሕዳሴው ግድብ ፋይዳ፦ "የሕዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ከተደመሩ አንጋፋ ሥራዎችን ጀምረው መጨረስ እንደሚችሉ ያሳየን የምሳሌነት ምልክት ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ። ✅ አረንጓዴ ዕድገት፦ ካለፈው ክፍለ ዘመን በተቃራኒ፣ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ጉዞ ተፈጥሮን የማይበክልና አህጉራዊ ትስስርን የሚያጠናክር እንደሆነ ተረጋግጧል። ኢትዮጵያ ዛሬ የምትጥለው መሠረት ለነገዋ አፍሪካ የብልፅግና ጮራ እና የታዳሽ ኃይል ማዕከልነቷ ዋስትና መሆኑ ተመላክቷል። #Ethiopia#LightOfAfrica#CleanEnergy#GreenDevelopment#GERD#AfricaRising#ኢትዮጵያ