EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
@ebcnewsnow · Post #52075 · 2026/03/05 19:48
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፡ ለዘላቂ ሰላምና ለጋራ ብሔራዊ ስምምነት አዲስ ምዕራፍ **************** የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ውስብስብ ፈተናዎችን እየተጋፈጠ፣ ሀገራዊ መግባባትን ለማስፈን የሚያስችሉ ተጨባጭ ሥራዎችን በትጋት እያከናወነ ይገኛል። በሂደቱ በዋናነት ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍል ያሳተፈ፣ አካታችና ተዓማኒ ለማድረግ የሚያስችሉ የዝግጅት ተግባራትን ቅድሚያ ሰጥቶ ሲያከናውን ቆይቷል። ኮሚሽኑ ጠንካራ ተቋማዊ አወቃቀርና የሕግ ማዕቀፍ በመዘርጋት ለሥራው ምቹ ሁኔታ ከመፍጠሩም ባለፈ፣ በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች ሕዝባዊ ተሳትፎን መሠረት ያደረገ የተሳታፊዎች ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን በስኬት አከናውኗል። #NationalDialogue#PeaceBuilding#ConflictResolution#NationalConsensus#EastAfrica#InclusiveDialogue