TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
Inhoud
Postinhoud
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለፕሬዝዳንት ረጅብ ጣይፕ ኤርዶዋን ደማቅ አቀባበል አደረጉ ******************* ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቱርክዬ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ረጅብ ጣይፕ ኤርዶዋን በኢትዮጵያ ለሚያደርጉት ይፋዊ ጉብኝት ዛሬ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው ተቀብለዋቸዋል። ይህ ጉብኝት በቱርክዬ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን እያደገ የመጣ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚያጎላ ሲሆን፤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ሚናም የሚያረጋግጥ ነው። #EthiopianBroadcastingCorporation#Ebcdotstream#Ethiopia#PMAbiy#RecepTayyipErdoğan#Turkiye#Diplomacy