TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) avatar

TGINSIGHT POST

Post #53631

@ebcnewsnow

EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)

Weergaven5,730Weergaven van post
Geplaatst16 apr16-04-2026, 15:00
Inhoud

Postinhoud

የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀምን፣ አስፈላጊውን የሕግ ማዕቀፍ በማበጀት፣ በአግባቡ መምራት ይገባል - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ********************** የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የመሩት የአፍሪካ ህብረት ሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት የሚኒስትሮች ስብሰባ በበይነ መረብ ተካሂዷል። ውይይቱ “ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ አስተዳደር፣ ሰላም እና ጸጥታ በአፍሪካ'' በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው። ስብሰባው በኢትዮጵያ የወሩ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት ሊቀመንበርነት ከሚከናወኑ ተግባራት አንዱ ነው። የስብሰባው መሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው፥ ሰው ሰራሽ አስተውሎት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአስተዳደር፣ የኢኮኖሚ ልማት እና ደኀንነት ጉዳዮችን በፍጥነት እየለወጠ መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥታት እና ተቋማት በውሳኔ አሰጣጥ፣ በሕዝብ አስተዳደር፣ በደኀንነት ሥርዓት እና በኢኮኖሚ ዕቅዳቸው ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በተቀናጀ መንገድ የመጠቀም ሁኔታቸው በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱን አንስተዋል። ሰው ሰራሽ አስተውሎት በአፍሪካ መልካም ዕድሎችን እና ስጋቶችን ጭምር ይዞ መምጣቱንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ዶ/ር ጌዲዮን በንግግራቸው፥ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በአግባቡ በመጠቀም የሚገኙ ትሩፋቶችንም አብራርተዋል። ግጭትን አስቀድሞ ለመከላከል የሚሠሩ ሥራዎችን በማጠናከር፣ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥራዎችን በመተግበር፣ የሽምግልና ጥረቶችን በመደገፍ እና በአጠቃላይ በአህጉሪቱ የአስተዳደር ሥርዓቶችን በማሻሻል ረገድ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለው ዘርዝረዋል። በሌላ በኩል የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም በአግባቡ ካልተመራ ሐሰተኛ መረጃዎችን በማስፋፋት እና የሳይበር ወንጀሎችን በማበራከት ለሽብርተኛ ድርጅቶች እና ተባባሪዎቻቸው ጥቅም ሊውል እንደሚችል ጠቁመዋል። በመሆኑም ለዘርፉ አስፈላጊውን የሕግ ማዕቀፍ ማበጀት እና ማጠናከር እንደሚገባ በአጽንኦት ገልጸዋል። #Ethiopia#MFA#Africa#AU#ArtificialIntelligence#AI#EBC