TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
← () => "翠楼屋"

TGINSIGHT SIMILAR POSTS

查找相似内容

Source channel @lambdaexpression · Post #310 · 2月13日

by iPhone13 Pro #摄影

Hashtags

Results

找到 12 条相似帖子

搜索 #animalwelfare

当前筛选 #animalwelfare清除筛选
#HaSab

@Hasab_2016 · Post #21 · 2023/09/10 20:52

#HaSab #animalwelfare ወደ አህያ ቄራ ጉዳይ ደግሞ እንምጣ! ቻይና ኢጃ'ኦ(Ejiao) የሚባል ባህላዊ መድሀኒት አላት። መድሃኒቱ ለደማነስ፣ ራስ መታወክ፣ የእንቅልፍ እጦት እና የወር አበባ መዛባት ፍትሁን ነው ተብሎ በተጠቃሚዎቹ ይታሰባል። የሚቀመመውም የአህያ ቆዳ በእሳት ተፈትኖ በሚገኘው ጄላቲን ነው። ኢጃ'ኦን ለማምረት ቻይና በአመት የ4.8 million አህዮችን እርድ ትፈልጋለች። ይህ አለም ካላት 55.5 million የአህዮች ብዛት አንጻር እጅግ የተጋነነ እና ጣርያ የነካ የፍላጎት መጠን ከ1990-2018(እ.አ.አ) የቻይናን የአህያ ብዛት ከ11.1 million ወደ 2.5 million እንዲሽቆለቁል አድርጎታል። የሀገሪቱ የመካከለኛ ገቢ ያለው ማህበረሰብ ክፍል የዚህ መድሃኒት ሁነኛ ፈላጊ መሆንና የመካከለኛው ኢኮኖሚ በቻይና ጥሩ መሻሻል በማሳየቱ ቁጥሩን አግዝፎታል። በተጨማሪም ቻይና በምርቱ ላይ ያላትን የቀረጥ መጠን መቀነሷ እና የኢንፖርት መጠን እንዲያድግ ማድረጓ እንዲሁም የመድሃኒቱ ዝነኛ መሆን ለፍጆታው መጨመር እንደምክንያት ይጠቀሳል። እ.አ.አ በ2017 አንድ ኪሎ ለኢዳ'ኦ የሚውል የአህያ ቆዳ በ830 የአሜሪካ ዶላር ተሽጧል። ከዚህ ውስጥ 90% የተገኘው ከሌሎች እንደ አፍሪካ ያሉ የአለም ክፍሎች ኤክስፖርት ከተደረገ አቅርቦት ነው። The gardian በ2019 እንዳወጣው ዘገባ ከሆነ ይህ ፍላጎት በዚህ ከቀጠለ በኢጃ'ኦ ምክንያት የአለም የአህያ ብዛት በአምስት አመት ውስጥ በግማሽ ይቀንሳል። ቻይና አህዮቻቸውን ፍለጋ የዳበሰቻቸውን ሀገራት ዳታ ስንመለከት ደግሞ:- -ጋና እ.አ.አ በ2013 የአህያ ቄራ ከፍታ እጅግ አሳሳቢ በሆነ መልኩ የአህያ ቁጥር መመናመን፣ ኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ በመስፋፋቱ በ2017 ዘግታለች። -በቦትስዋና የአህያ ቆዳ ኤክስፖርት መጀመሩን ተከትሎ 60% የአህያ ቁጥር ቀንሷል። -ታንዛኒያ ጫናውን ለመቋቋም ለ10 አመት የአህያ እርድን ከሀገሯ አግዳለች። -ናይጄርያ የኢጃ'ኦ ምርት በህጋዊም በህገወጥም መንገድ ጥሬ እቃ የሚያገኝባት ማዕከል ሆናለች -ጎረቤት ሀገር ኬንያ ደግሞ ከቻይና ጋር ይህንን ንግድ ለማሳለጥ የሁለትዮሽ ስምምነት አላት። እነዚህ ሀገራት ቀጣይ እጣ ፋንታዎቻቸው ምን የሚሆን ይመስላችኋል? ይህ ንግድ ጉዳቱ ወይንስ ጠቀሜታው ይጎላል? የሀገራችንን ጉዳይ ደግሞ በመጨረሻ ጽሑፌ እንመለከታለን። ያሬድ ኤርሚያስ 3rd year DVM student, AAU-OHC Founder and secretary, Membership director of Rotaract club of Kuriftu.

#HaSab

@Hasab_2016 · Post #19 · 2023/09/10 20:51

#HaSab #Animalwelfare 1.4 Billion ዶላር አመታዊ ፋይዳ! ባለፈው "ከቻይና እንበልጣለን" በሚል ርዕስ አንድ ጽሑፍ አጋርቼ ነበር። ጽሑፉ በሀገራችን ያለውን የአህያ መረጃ እንዲሁም የDonkey sanctuary አመሠራረት ለመዳሰስ ሞክርያለሁ። በዛሬው ጽሑፍ ደግሞ የአህያ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እና በአሰላ ከተማ የተገነባው የአህያ ቄራን ሁኔታ ለመመልከት እንሞክር። በሀገራችን አብዛኛው የእርሻ ቦታ እና የመኖርያ መንደር እጅግ የተራራቀ ነው። ገበሬው በለሊት ተነስቶ በሬውን፣ ሞፈር እና ቀንበሩን ይዞ ሌሎች በእርሻው ወቅት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በአህያው ጀርባ አኑሮ ወደ እርሻው ይሄዳል። ቡቃያው አፍርቱ እህሉ እስኪደርስ ድረስ ለሚያከናውናቸው ተግባራት የሚጠቀማቸውን መሠርያዎች የምትሸከምለት አህያው ነች። በተጨማሪም አዝመራ በደረሰ ጊዜ አህያ የእውቅያ ስርዓቱ ላይ ትልቅ ሚና አላት።(የህዳር አህያን ታውቃላችሁ? ህዳር አዝመራ የሚደርስበት ወቅት እንደመሆኑ የህዳር አህያ ለመንደሩ ሰው ሁሉ ግልጋሎት ትሰጣለች። አህያዬን ለምን ወሰድክ የለም!) ስለዚህ አንዲት አህያ ከእርሻ እስከ ጎተራ መሙላት ድረስ ፋይዳዋ ብዙ ነው። የሀገሬ ገበሬ "አህያዬ ባትኖር እኔ ና ሚስቴ አህዮች ነበርንን ይላል።" ሸክማችን ሸክሟ ሆኖ ነው እንደሰው ያለ ሸክም የምራመደው ማለቱ ነው። በተጨማሪም በሀገራችን ጉራማይሌ መልከዓ ምድር የቆላን ምርት ለደጋ የደጋውን ለቆላ ለማድረስ የአህያ ማጓጓዣ መጠቀም ግዴታ ነው። ገና መሠረተ ልማት በየደጃፋችን የደረሰልን ሀብታም ሀገር አይደለንም። እጅግ ብዙ ይቀረናል። የአቀበት ቁልቁለት ስቃይን ተቋቁሞ እንደ አህያ የተሸከመልን ቴክኖሎጂ የለም። መሠረተ ልማት ቢሟላልን እንኳ የነዳጅ ነገር እንኳን ለገጠሩ ለከተማውም ከአቅም በላይ ነው። እጅ ላይ ያለች ብቸኛ አማራጭ ነች አህያ። ቅዳሜ ገበያ ሄዶ ሊሸምት ያሰበ ከአህያ ጀርባ ላይ ሸክም ሲወርድ ሳያይ አይመለስም። ይህ ብቻ ሳይሆን በገጠር ከተማዎች የእለት ጉርሳቸው በአህያ ጋሪ ጭነት የሚጎርሱ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። የአንዲት አህያ በቤት ውስጥ መኖር ለሴቶች፣ለአቅመ ደካሞች እና ህፃናት ፍይዳው ብዙ ነው። አንድ በሬ ሊጠቀምበት የሚችለው የቤቱ አባወራ ብቻ ነው። ነገር ግን አንዲት አህያ ለአባወራው እህል በመውቃት፣ በመሸከም እና በማጓጓዝ ብታግዝ ለእማወራይቱ ደግሞ ወሃ ከሩቅ ቀድቶ በመምጣት፣ ለማገዶ እንጨት ለቅሞ ለማምጣት፣ በጓሮ ተክለው ያጸደቁት አትክልት ጀርበቸው ሳይጎብጥ የሚፈለገው ቦታ ወስዶ ለመሸጥ ግልጋሎት ይሰጣሉ። የግል ገቢም ይኖራቸዋል። እቤቱ አህያ ያለ ህፃናት "ወሃ ከምንጭ ሳትቀዳ ወደ ትምህርት ቤት አትሄድም!" አይባልም። ጉልበቱ በመጠኑም ቢሆን ከመበዝበዝ ያርፋል። ለማጥናት ጊዜ ይኖረዋል። ለአቅመ ደካሞችም የለት ገቢያቸው ጥቂት ለሆነ የአህያ ጭነት መተዳደርያ ነው። ስለዚህ አህያዎች እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገራት በተለይም ለገጠርራማይቱ ክፍል እጅግ ጠቃሚ ናቸው። ሰዎች እና ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ፣ ለእርሻ እና ውቅያ፣በተጨማሪም በተለያዩ የግንባታ ስራዎች ወቅት የግንባታ እቃዎች ለማጓጓዝ ያገለግላሉ። ከሌሎች የትራንስፖርት አማራጮች አንጻር(እንደ መኪና) ዋጋቸው ርካሽ መሆኑ በቀላል በታችኛው የኑሮ እርከን ያሉ ሰዎች እንዲያገኟቸው እና እንዲጠቀሙባቸው ያደርጋል። ይህ ችላ የሚባል ኢኮኖሚያዊ ጥቅም አይደለም። አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያሳዩት አህያ ለኢትዮጵያ GDP 1.4 Million የአሜሪካ ዶላር አመታዊ ፋይዳ አላት። አሁን ባለው የእንስሳት ደህንነት ደረጃ እና የግብርና አቅም ይህን ያህል ከፈየደ ይበልጥ ብናድግ እና ብንሻሻል ፋይዳው ምን ይህል ይሆን? እንቀጥላለን ያሬድ ኤርሚያስ 3rd year DVM student, AAU-OHC Founder and secretary, Membership director of Rotaract club of Kuriftu.

#HaSab

@Hasab_2016 · Post #17 · 2023/09/10 20:48

#HaSab #Animalwelfare ከቻይና እንበልጣለን! በኢትዮጵያ በተለይም በገጠራማው አከባቢ ከሦስት አባወራዎች አንዱ አህያ እንዳለው ይታመናል። የሀገራችን የአህያ ዝርያ በአራት የሚከፈል ሲሆን እኚህ ዝርያዎች ጅማ፣ አቢሲኒያ፣ ኦጋዴን እና ሰናር የሚባሉ ሲሆን፤ በሀገሪቱ በቆላ፣ደጋ እንዲሁም በተለያዩ የምድሪቱ የተፈጥሮ ሁኔታዎች ጋር ስሙሙ ሆነው ይኖራሉ።እ.ኢ.አ በ2013 በFAO በተሰራ ጥናት መሠረት ኢትዮጵያ የ7 million አህዮች መገኛ ናት። የቅርብ መረጃዎች ደግሞ ቁጥራቸው እስከ 8.5 million ሊደርስ እንደሚችል ይናገራሉ። ይህ ቁጥር ቻይናን በማስከተል በአለም ትልቅ ቁጥር ያላት ሀገር ያደርጋታል።(ከቻይና የምንበልጠው እንግዲህ በቁጥር ነው!) አህያ የፈረስ ቤተሰብ የሆነው Family Equidae አባል ነች። አመቱን ሙሉ መራባት ትችላለች። በእንክብካቤ እና በደህንነት መያዝ ከተቻለ እስከ 30 አመት ትኖራለች።(በኢትዮጵያ በአማካይ ከ4-6 ዓመት ብቻ ነው የምትኖረው)። ደረሰች የምትባልበት እድሜ ከ2-3 ዓመት ሲሆን በዚህ ግዜ ጥሩ የሚባለው የሰውነት ክብደት 105kg ነው።እህች ጠንካራ እና ብርቱ ፍጥረት ጥሩ የማስታወስ ችሎታ አላት።የተጓዘችበትን መንገድ በፍጹም አትረሳም።(የሀገር ሰው ሲተርት "የምትሄድበት መንገድ ቢጠፋህ አህያህን ተከተል።" ይላል።) የሸሆና ጥፍራቸው ጠንካራ መሆን እና አስቸጋሪ መንገዶችን ተጋፍጠው መጓዝ መቻላቸው ከሌሎች የፈረስ ቤተሰቦች ይልቅ ለሸክም እና ለማጓጓዣነት ተመራጭ አድርጓቸዋል በኢትዮጵያ አንዲት አህያ ከ6-100kg(አንዳንዴም ከዛ በላይ) ተሸክማ ከ15-20 km ያክል ርቀት ከ5-6 ሰዓታት ያለ እረፍት ልትጓዝ ትችላለች። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የምድር ወገብ ሀሩር አውራጃዎች(Tropical region) አህዮች በብዛት በመንጋጋ ቆልፍ (tetanus)፣ ተዋስያን(internal and external parasites)፣ ወበቅ(intense heat)፣ በተለያዩ የመቁሰል አደጋዎች( Traumatic injury)፣ ተገቢ የሆነ አመጋገብ እጥረት እና የሸሆና ጥፍራቸው ከመጠን ያለፈ በማደጉ ለሚመጡ ችግሮች ተጋላጭ ናቸው። በተለይም በሸክም መብዛት እና ከመጠን ያለፈ ድብደባ የሚቆስሉ እና የሚሰቃዩ አህዮች ቁጥር ቀላል አይደለም። Donkey sanctuary በአዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ የእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይገኛል። Donkey sanctuary እ.አ.አ በ1969 ኤልሳቤት ሳፈንድሰን በተባለች የእንስሳት ደህንነት አቀንቃኝ በእንግሊዟ ዴቮን ተመሥርቷል።ሲቋቋም ዋና አላማው ለአህዮች ደህንነት ምቹ የሆነ ከባቢን መፍጠር የነበረ ቢሆንም፤ በአሁኑ ወቅተ በአውሮፓ፣አፍሪካ እና አሜሪካ ውስጥ በአህዮች ደህንነት ጥበቃ፣ በእንስሳት ደህንነት ግንዛቤ ማስጨበጥ እንዲሁም የተለያዩ ባለሞያዎችን ማስተማርና ማሰልጠን ላይ አበክሮ ይሰራል። ቅርንጫፉም በ40 ሀገራት ውስጥ ይገኛል። Donkey sanctuary በኢትዮጵያ እ.ኢ.አ በ1986 ዓ.ም በፕሮፌሰር ፍሰሃ ገ/አብ አማካኝነት ተመስርቶ እየሰራ ይገኛል።

#HaSab

@Hasab_2016 · Post #13 · 2023/09/10 20:20

#HaSab #Animalwelfare The way to independence እ.አ.አ በ1908 ናሽቪል በምትባል የአሜሪካ ከተማ ውስጥ ሞሪስ ፍራንክ(Morris Frank) የሚባል ሰው ተወለደ። ይህ ሰው ልጅነቱን ያሳለፈው ማየት የተሳናት እናቱን በመርዳት እና በምትጓዝበት መንገድ ሁሉ አይኗ በመሆን ነው። ነገር ግን በስድስት አመቱ በፈረስ ጀርባ ላይ ሆኖ ሽምጥ ሲጋልብ የቀኝ አይኑን የዛፍ ቅርንጫፍ ጠነቆለው። አንድ አይኑን አጣ። በአስራ ስድት አመቱ ደግሞ ሌላኛው አይኑ በቡጢ ፈሰሰ። ፍራንክ ማየት የተሳነው ሆነ። ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገባ ሊለምድ ያልቻለው እና ሁሌ ይማረርበት የነበረው ማየት የተሳነው በመሆኑ ሁሌም የሰዎችን እርዳታ መፈለጉ ነበር። ብቻውን ያሻው ቦታ ብድግ ብሎ ባለመሄዱ እጅግ ያዝን ነበር። ይባስ ብሎ የእድሜ እኩዮቹ የሚፈልገውን ቦታ እንዲወስዱት በጠየቀ ጊዜ ታማኝ ተባባሪ ሊሆኑ አልቻሉም።ህይወት እጅግ ከብዳው ነበር።አንድ ዜና ሲነበብ እስኪሰማ ድረስ። በህዳር 1927(እ.አ.አ) የፍራንክ አባት የቅዳሜ ምሽት ዜናን ሲያነብለት የሰማው ነገር ግን ህይወቱን እስከወዲያኛው ቀየረ። በርግጥ ያ ዜና የፍራንክን ብቻ ሳይሆን በአለም ላይ ያሉ እጅግ በርካታ ማየት የተሳናቸው ሰዎች ህይወትም የለወጠ እጅግ አስደሳች ዜና ነበር። ነገሩ እንዲህ ነው። በአሜሪካዊቷ የውሾች አሰልጣኝ ድሮቲ ሒርሰን አውስተስ(Dorothy Harrison Eustis) ጀርመን ውስጥ የተከፈተ ትምህርት ቤት በመጀመርያው የአለም ጦርነት አይናቸውን ያጡ የዘመቻ ተመላሾች ከአጋዥ ውሾች ጋር ሆነው መሥራት እንዲችሉ የሚያደርግ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን የሚያበስር ዜና ነበር። ፍራንክ ይሄን ሲሰማ ጊዜ ሳያጠፋ ለአውስተስ ጻፈላት። ህይወቱ ውስጥ ታማኝ የሆነው እና ወዲህ እንሂድ ወዲያ ቢል የማይሰለቸው አጋዥ ጋር መሠልጠን እንደሚፈልግ ነገራት። እሷም ሲውዘርላድ ወደሚገኘው ትምህርት ቤት እንዲሄድ የእድል በር ከፈተችለት። ሲውዘርላንድ እንደደረሰ 'kiss' የምትባል ውሻ ተሰጠችው። ይህችን እስከ ህይወቱ ፍጻሜ ባጣቸው አይኖች ፈንታ አይን ሆነ የኖረችን ታማኝ ፍጥረት ፍራንክ 'buddy' ብሎ ሰየማት። ፍራንክ እና ባዲ አብረው 50,000 ማይሎችን ተጉዘዋል። ይህም ውሾች ማየት የተሳናቸውን ሰዎች እንዴት ሊያገዙ እና በህይወታቸው ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚችሉ ለአለም አስመስክሯል። ባዲ እጅግ አስደናቂ በሆነ መልኩ የፍራንክን የየእለት ጉዞ አይን ሆና ከመምራት አልፋ እ.አ.አ በ1938 ለመጀመርያ ጊዜ ከቺካጎ ወደ ኒዎዮርክ ለሚደረገው በረራ ሙሉ አጃቢው ሆና በነጻነት የማንንም እርዳታ ሳይጠይቅ እንዲጓዝ አድርጋዋለች። ይህ ስራዋ አለም የውሾች ለማየት የተሳናቸው ሁነኛ አጋዥ መሆንን ሙሉ በሙሉ እንዲስማማ እና እንዲደግፍ ያደረገ ሆኗል። በባዲ ይህወቱ የቀለለት ፍራንክ ታድያ እጁን አጣጥፎ አልተቀመጠም። እ.አ.አ በ1929 ከአውስተስ ጋር በመሆን በአሜሪካ የመጀመርያውን የማየት የተሳናቸው አጋዥ ውሾች ማሰልጠኛ (The seeing eye) ከፍቷል።ምክትል ፕሬዝደንት በመሆንም አገልግሏል። በተጨማሪም በተገኘባቸው ስፍራዎች ሁሉ ስለ ውሾች እና ማየት የተሳናቸው ሰዎች ቁርኝት 'The divine gift of freedom' እያለ ለማስተማር ጥሯል። ዛሬ ላይ እንደ International Association of Assistance Dog Partners(IAADP) ዌብሳይት ገለጻ ከሆነ በአሜሪካ 100,000 ገደማ Assistant dogኦች ለተለያዩ አካልጉዳተኛች አጋዥ ጓደኛ ናቸው። ማየት ለተሳነው አይን፣መስማት ለተሳነው ጆሮ፣መንቀሳቀስ ለከበደው ተላላኪ እንዲሁም የአእምሮ ህመም ላጋጠመው እንደ ቴራፒ ሆነው ያገለግላሉ። በሀገራችን ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ደግሞ ከ5000 ያላነሱ ውሾች ይገኛሉ። ገና ሰዎች ሲያዩዋቸው አርፈው በተኙበት ድንጋይ ይወረውሩባቸዋል። በሽታ ያስተላልፉብናል በሚል ሰበብ ሰቅለው ገድረው የሙት በድን አፋቸው ድንገይ አነጣጥሮ መጨመር ይጫወቱባቸዋል።በሀገራችን የእንስሳትን ደህንነት መጠበቅ እጅግ ቅንጦት ነው።በጥቂት ግለሰቦች ደረጃ ካልሆነ በቀር እንደ ሀገር ለእንስሳት ደህንነት ብዙ አላሰብንም፣አልተጨነቅንም። ከሌላው አለም ተምረን ተንከባክበናው ይበልጥ እንዲጠቅሙን ለማድረግ ለምን ተሳነን ይሆን? ፍራንክ እና ባዲ በ Morristown Green, New Jersey በቁመናቸው ልክ የሚሆን(life sized) የነሃስ ሐውልት እ.አ.አ በ2005 ሁሌ በሚመላለሱበት መንገድ አቅራብያ ተሰርቶላቸዋል። (ምስሉ ኮመንት ውስጥ አለ) እንዲህ ያለ ታሪክ ስሰማ ለሀገሬ እቀናለሁ! ያሬድ ኤርሚያስ 3rd year DVM student, AAU-OHC Founder and secretary, Membership director of Rotaract club of Kuriftu.

Google Facts™ [ ️@googlefactss🌎]

@googlefactss · Post #40739 · 2026/03/05 15:01

Sheep can feel emotions like fear, anger, boredom, and happiness. They evaluate their surroundings using checks like suddenness, familiarity, predictability, and control, similar to humans. Sudden events can cause fear, while predictable environments may lead to boredom. 🐑⚽️ @googlefactss #AnimalWelfare#Sheep#Emotions#AnimalCare#Nature

EKOLOG.UZ| ENG

@ekologuzenglish · Post #11611 · 2026/02/15 01:02

🇳🇴 NORWAY PHASES OUT UNNATURALLY FAST-GROWING “FRANKEN-CHICKENS” Norway has announced a gradual phase-out of so-called “franken-chickens” by 2027. Norway, where about 70 million chickens are raised annually for food production, has become the first country to commit to raising 100% of its poultry under conditions that ensure high animal welfare standards. Animal rights advocates have welcomed the decision, calling it a “historic moment.” “Franken-chickens,” often referred to in Norway as “turbo-chickens,” are fast-growing birds bred through selective breeding to reach maximum weight in the shortest possible time. Due to rapid growth and extreme size, these chickens suffer from numerous health problems, and most animal welfare organizations strongly condemn this practice. According to Humane World for Animals, franken-chickens reach their “slaughter weight” in just six weeks, leading to severe strain on their bones, muscles, and ligaments. Their bodies often begin to break down as they grow, and many birds lose the ability to move. Humane League UK describes their lives as “extremely short and painful.” The animal protection coalition Anima International has been campaigning for five years to eliminate fast-growing chicken breeds in Norway. Several animal welfare groups are also calling for similar measures in the United Kingdom. Experts emphasize that this decision marks a significant step forward in improving animal welfare. #AnimalRights#Norway#AnimalWelfare#PoultryFarming#ProtectAnimals ☘️Read the latest environmental news on the @ekologuz page. Follow us and send your suggestions and wishes via @eklguz_bot Instagram | Facebook | Twitter | Sayt | Youtube

Animal Welfare Club

@animalwelfarewecare · Post #99 · 2026/02/19 08:20

🐾 WEBINAR ALERT: Rabies Elimination and Animal Welfare 🐾 Join us for a focused, hard-hitting session featuring leading voices in veterinary medicine, public health, and youth advocacy. Our expert panel will break down the most pressing issues, from emergency shelter response to global rabies elimination strategies. 📅Date: Feb 19 ⏰Time: 2:30 L.T 📍Platform: t.me/aau_ohc 🎤MEET THE PANELISTS: 🔹 Dr. Mesfin Semu Wodajo Graduate of Moscow Veterinary Academy (1994) and Utrecht University (2000). Former Associate Researcher at Tetracore, LLC. 14 years as Chief of Staff at Banfield Pet Hospital. Currently Medical Director & Owner at Upper Marlboro Veterinary Hospital. 🔹 Dr. Alazar Ayele Veterinarian specializing in mobile pet care. Co-founder of Beyond Student for Change initiative. Operates a mobile veterinary clinic to expand access to professional animal healthcare and leads community-based stray dog mass rabies vaccination campaigns. 🔹 Dr. Biruk Eshetu University of Gondar graduate (2015 E.C.). Former founder & president of One Health Innovation Club and VP of Clinical Medicine Club at UoG. Currently Manager of the Animal Welfare and Protection Trauma Shelter, Addis Ababa, where he works extensively with pets and shelter animals. 🔹 Yared Ermiyas DVM Candidate, Co-founder of AAU One Health Club, and Animal Welfare Advocate. 🎙️Format:Live 📲 Set a reminder and join us! 👇 Drop a "👋" in the comments if you'll be there! #RabiesElimination#AnimalWelfare#OneHealth#YouthAdvocacy#Webinar#VeterinaryMedicine#ShelterAndRescue

EKOLOG.UZ| ENG

@ekologuzenglish · Post #10564 · 2025/11/30 13:03

The UK government has unveiled an unprecedented plan to gradually eliminate animal testing in medical and pharmaceutical research. The first phase will begin at the end of 2026 and will eliminate tests on mice used to develop treatments for skin and eye irritations. Additionally, the country has committed to reducing the use of dogs and primates in laboratories by 35% by 2030, fulfilling an election promise made by the Labour Party. Backed by £60 million, the strategy aims to promote ethical and technologically advanced alternatives that replace animal models without compromising the safety of vaccines, medicines, or pesticides. Although animal experiments peaked in 2015 — with over 4 million animals used — advances in alternative methods had already helped reduce that number. However, progress has stalled in recent years, so this new initiative seeks to accelerate the full replacement of animals. Science Secretary Patrick Vallance stated, “Nobody wants to witness animal suffering,” and the new roadmap will allow governments, companies, scientists, and animal welfare organizations to collaborate on faster and more effective solutions. Part of the investment will go to a specialized center that will integrate technology, data, and expertise to accelerate the transition to animal-free science. 🐾 Do you think Uzbekistan should implement a similar plan to reduce and replace animal testing? 🇺🇿💭 #AnimalWelfare#AnimalFreeScience#UK#AnimalTesting#ScientificInnovation#LabAnimals#ADNMascotas#AnimalNews#AnimalProtection#OneHealth☘️Read the latest environmental news on the @ekologuz page. Follow us and send your suggestions and wishes via @eklguz_bot Instagram | Facebook | Twitter | Sayt | Youtube.

Venture Village Wall 🦄

@venturevillagewall · Post #3718 · 2024/12/26 07:00

Vitalik Buterin Donates to Thai Zoo Ethereum co-founder Vitalik Buterin donates 10 million Thai baht (~$292,230) to Khao Kheow Zoo, Thailand. The donation, in two installments, starts December 26, 2024. Buterin and family will be adopted by the zoo. Details: Khao Kheow Zoo Announcement #VitalikButerin#Ethereum#KhaoKheowZoo#Donation#Crypto#Blockchain#Thailand#AnimalWelfare#Charity#Adoption#Philanthropy#Zoo#MOODENG#CommunitySupport#TechForGood#EthereumCoFounder#News