የቅርብ ጊዜ ልጥፎች
ገጽ 14 ከ 15 · 169 ልጥፎች
#HaSab #Animalwelfare The way to independence እ.አ.አ በ1908 ናሽቪል በምትባል የአሜሪካ ከተማ ውስጥ ሞሪስ ፍራንክ(Morris Frank) የሚባል ሰው ተወለደ። ይህ ሰው ልጅነቱን ያሳለፈው ማየት የተሳናት እናቱን በመርዳት እና በምትጓዝበት መንገድ ሁሉ አይኗ በመሆን ነው። ነገር ግን በስድስት አመቱ በፈረስ ጀርባ ላይ ሆኖ ሽምጥ ሲጋልብ የቀኝ አይኑን የዛፍ ቅርንጫፍ ጠነቆለው። አንድ አይኑን አጣ። በአስራ ስድት አመቱ ደግሞ ሌላኛው አይኑ በቡጢ ፈሰሰ። ፍራንክ ማየት የተሳነው ሆነ። ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገባ ሊለምድ ያልቻለው እና ሁሌ ይማረርበት የነበረው ማየት የተሳነው በመሆኑ ሁሌም የሰዎችን እርዳታ መፈለጉ ነበር። ብቻውን ያሻው ቦታ ብድግ ብሎ ባለመሄዱ እጅግ ያዝን ነበር። ይባስ ብሎ የእድሜ እኩዮቹ የሚፈልገውን ቦታ እንዲወስዱት በጠየቀ ጊዜ ታማኝ ተባባሪ ሊሆኑ አልቻሉም።ህይወት እጅግ ከብዳው ነበር።አንድ ዜና ሲነበብ እስኪሰማ ድረስ። በህዳር 1927(እ.አ.አ) የፍራንክ አባት የቅዳሜ ምሽት ዜናን ሲያነብለት የሰማው ነገር ግን ህይወቱን እስከወዲያኛው ቀየረ። በርግጥ ያ ዜና የፍራንክን ብቻ ሳይሆን በአለም ላይ ያሉ እጅግ በርካታ ማየት የተሳናቸው ሰዎች ህይወትም የለወጠ እጅግ አስደሳች ዜና ነበር። ነገሩ እንዲህ ነው። በአሜሪካዊቷ የውሾች አሰልጣኝ ድሮቲ ሒርሰን አውስተስ(Dorothy Harrison Eustis) ጀርመን ውስጥ የተከፈተ ትምህርት ቤት በመጀመርያው የአለም ጦርነት አይናቸውን ያጡ የዘመቻ ተመላሾች ከአጋዥ ውሾች ጋር ሆነው መሥራት እንዲችሉ የሚያደርግ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን የሚያበስር ዜና ነበር። ፍራንክ ይሄን ሲሰማ ጊዜ ሳያጠፋ ለአውስተስ ጻፈላት። ህይወቱ ውስጥ ታማኝ የሆነው እና ወዲህ እንሂድ ወዲያ ቢል የማይሰለቸው አጋዥ ጋር መሠልጠን እንደሚፈልግ ነገራት። እሷም ሲውዘርላድ ወደሚገኘው ትምህርት ቤት እንዲሄድ የእድል በር ከፈተችለት። ሲውዘርላንድ እንደደረሰ 'kiss' የምትባል ውሻ ተሰጠችው። ይህችን እስከ ህይወቱ ፍጻሜ ባጣቸው አይኖች ፈንታ አይን ሆነ የኖረችን ታማኝ ፍጥረት ፍራንክ 'buddy' ብሎ ሰየማት። ፍራንክ እና ባዲ አብረው 50,000 ማይሎችን ተጉዘዋል። ይህም ውሾች ማየት የተሳናቸውን ሰዎች እንዴት ሊያገዙ እና በህይወታቸው ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንደሚችሉ ለአለም አስመስክሯል። ባዲ እጅግ አስደናቂ በሆነ መልኩ የፍራንክን የየእለት ጉዞ አይን ሆና ከመምራት አልፋ እ.አ.አ በ1938 ለመጀመርያ ጊዜ ከቺካጎ ወደ ኒዎዮርክ ለሚደረገው በረራ ሙሉ አጃቢው ሆና በነጻነት የማንንም እርዳታ ሳይጠይቅ እንዲጓዝ አድርጋዋለች። ይህ ስራዋ አለም የውሾች ለማየት የተሳናቸው ሁነኛ አጋዥ መሆንን ሙሉ በሙሉ እንዲስማማ እና እንዲደግፍ ያደረገ ሆኗል። በባዲ ይህወቱ የቀለለት ፍራንክ ታድያ እጁን አጣጥፎ አልተቀመጠም። እ.አ.አ በ1929 ከአውስተስ ጋር በመሆን በአሜሪካ የመጀመርያውን የማየት የተሳናቸው አጋዥ ውሾች ማሰልጠኛ (The seeing eye) ከፍቷል።ምክትል ፕሬዝደንት በመሆንም አገልግሏል። በተጨማሪም በተገኘባቸው ስፍራዎች ሁሉ ስለ ውሾች እና ማየት የተሳናቸው ሰዎች ቁርኝት 'The divine gift of freedom' እያለ ለማስተማር ጥሯል። ዛሬ ላይ እንደ International Association of Assistance Dog Partners(IAADP) ዌብሳይት ገለጻ ከሆነ በአሜሪካ 100,000 ገደማ Assistant dogኦች ለተለያዩ አካልጉዳተኛች አጋዥ ጓደኛ ናቸው። ማየት ለተሳነው አይን፣መስማት ለተሳነው ጆሮ፣መንቀሳቀስ ለከበደው ተላላኪ እንዲሁም የአእምሮ ህመም ላጋጠመው እንደ ቴራፒ ሆነው ያገለግላሉ። በሀገራችን ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ደግሞ ከ5000 ያላነሱ ውሾች ይገኛሉ። ገና ሰዎች ሲያዩዋቸው አርፈው በተኙበት ድንጋይ ይወረውሩባቸዋል። በሽታ ያስተላልፉብናል በሚል ሰበብ ሰቅለው ገድረው የሙት በድን አፋቸው ድንገይ አነጣጥሮ መጨመር ይጫወቱባቸዋል።በሀገራችን የእንስሳትን ደህንነት መጠበቅ እጅግ ቅንጦት ነው።በጥቂት ግለሰቦች ደረጃ ካልሆነ በቀር እንደ ሀገር ለእንስሳት ደህንነት ብዙ አላሰብንም፣አልተጨነቅንም። ከሌላው አለም ተምረን ተንከባክበናው ይበልጥ እንዲጠቅሙን ለማድረግ ለምን ተሳነን ይሆን? ፍራንክ እና ባዲ በ Morristown Green, New Jersey በቁመናቸው ልክ የሚሆን(life sized) የነሃስ ሐውልት እ.አ.አ በ2005 ሁሌ በሚመላለሱበት መንገድ አቅራብያ ተሰርቶላቸዋል። (ምስሉ ኮመንት ውስጥ አለ) እንዲህ ያለ ታሪክ ስሰማ ለሀገሬ እቀናለሁ! ያሬድ ኤርሚያስ 3rd year DVM student, AAU-OHC Founder and secretary, Membership director of Rotaract club of Kuriftu.
Hashtags
ታትሟል ሴፕቴ 10
#HaSab #Veteducation የሀይስኩል ተማሪዎች ስለ እኛ ምን ያስባሉ? ዛሬ የበጎ አድራጎት ስራዎችን በምሰራበት የኩሪፍቱ ሮትራክት ክለብ አማካኝነት ከ2ተኛ ደረጃ እና መሠናዶ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጋር በ profession day መገናኘት ችዬ ነበር። የመርሃ ግብሩ ዋነኛ አላማ ተማሪዎች መሆን የሚፈልጓቸው ፊልዶች እና የስራ መስኮች ውስጥ ያሉ እና እየተማሩ የሚገኙ ሰዎች ስለ ሞያው መጠየቅ የሚፈልጓቸውን ጥያቄዎች በመጠየቅ ተጨባጭ ምላሽ እንዲያገኙ ማድረግ ነበር። እኔ የእንስሳት ህክምና ተማሪዎችን(DVM) በመወከል ከጎኔ የምትመለከቷት ምዕራፍ ተወልደ ደግሞ የእንስሳት ህክምና ላቦራቶሪ ቴክኖሎጂ(VLT) ተማሪዎችን በመወከል ተገኝተናል። በዝግጅቱ ላይ ከተገኙት ተማሪዎች እጅግ ጥቂት የሚባሉት ወደ እኛ በመምጣት ስለ እንስሳት ህክምና ለማወቅ ፍላጎት ያሳዩ ሲሆን፤ የጥያቄዎቻቸው ይዘት እና ማወቅ የሚፈልጉት ከዚህ በማስከትል የዘረዘርኳቸው ሆነው አግኝተናል። -የእንስሳት ህክምና ክትባት ከመስጠት ውጪ ምንድነው የሚሰራው? -የእንስሳት ህክምና ከሰዎች ህክምና የሚለየው ምንድነው? -የእንስሳት ሀኪም ሰውን ማከም ይችላል? -የእንስሳት ህክምና ትምህርት ጊዜ የሚፈጀው ምን ያህል ነው? -እኔ የእንስሳት ሀኪም መሆን እፈልጋለሁ ግን የእንስሳት ሀኪሞች ደግሞ ብር ብዙ አያገኙም! -ሰዎች ያን ያክል ትኩረት ሰጥተው እንስሳን ያሳክማሉ? -በውሻ ተነከስን ስንል ሀኪሞች ውሻው አምጡት የሚሉን ለምንድነው? በአጠቃላይ ለተጠየቅናቸው ጥያቄዎች የእንስሳት ጤና ዘርፍ የስራው መስክ ሰፊ እና ጉራማይሌ መሆኑን አውስተን በአጭሩ ለመረዳት፤ የክሊኒክ ስራዎች(Clinical practice)፣የስነ ህይወት ጤና ምርምሮች(biomedical researches)፣ ትምህርት(education)፣ የላቦራቶሪ ምርመራዎች(diagnostic laboratory)፣ የማማከር ስራ(consultation)፣የሀገርን የምግብ ደህንነት እና አቅርቦት ማሳለጥ( safeguarding our nations food safety and supply)፣እና የህብረተሰብ ጤና(public health) የትኩረት አቅጣጫቸው መሆኑን ለማስረዳት ሞክረናል። ከነበረን ቆይታ እንደተረዳነው የሚመጣው ትውልድ ስለ እንስሳት ህክምና በወፍ በረረር ከመስማት ውጪ ገና በበቂ እንዳላወቀው እና አሁን ያለውጰባለሞያ ያለበት የኑሮ ሁኔታ ወደፊት እኔም ብገባ እንዲህ ነው የምሆነው የሚል ስጋት እንዳለው ተረድተናል። በተጨማሪም ሰዎች በግል የሚሰሯቸው የእንስሳት እርባታ እና መሰል ስራዎች በሌሎች የዘርፉ ባለሞያ ባልሆኑ ሰዎች በሰፊው እንደመሠራታቸው እንዲህ ያለው ስራ አላማ ተይዞለት ለትምህርት እንደሚገባ ግንዛቤው ያለ አይመስለኝም። ለእንሰሳት ያላቸው ርህራሄ እና ፍቅር ግን እጅግ አስደሳች መሆኑን በሚያወሩን ጊዜ መታዘብ ችለናል(ስለ ውሾቻቸው ሲያወሩ ፊታቸው ላይ ያለው ፈገግታ ይማርካል) ስለዚህ በሞያችን ውስጥ ንቁ እና ደስተኛ ብሎም አርአያ የሚሆን ባለሞያ እንዲኖር። መጪው ትውልድ ከተቀዳሚ ምርጫዎቹ መካከል የእንስሳት ጤና ዘርፍ እንዲኖር የሚከተሉት ጉዳዮች ትኩረት ቢሰጥባቸው እላለሁ። -የእንስሳት ጤና ባለሞያው በይበልጥ የሚሻሻልበት እና ዘርፉ ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ ቢሆን -በግል ሴክተር ውስጥ ጠንካራ ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉ የእንስሳት ጤና ዘርፍ ምሩቃንን ማፍራት -በእያንዳንዱ ወረዳ የሚገኝ የእንስሳት ሀኪምና ባለሞያ የደሞዝ እና ደረጃ እድገት ቢሻሻል -ጥሩ ስነ ምግባር እና ሞያ አክባሪነት ያለው አርአያ መሆን የሚችል ማፍራት። እኚህን ጉዳዮች ትኩረት አድርጎ መሥራት የእንስሳት ጤና ዘርፍ ለሚመጣው ትውልድ በልበሙሉነት የሚመርጠው ሞያ እንዲሆን ማድረግ እንደሚችል ልባዊ እምነቴ ነው። ያሬድ ኤርሚያስ 3rd year DVM student, AAU-OHC Founder and secretary, Membership director of Rotaract club of Kuriftu.
Hashtags
ታትሟል ሴፕቴ 10
#HaSab #Exportmarket እያለ እንደሌለ! * ጥሩ መሠረት ያለው ነገር በሚገባ ሳይሰራበት ሲቀር እና ትከሉረት ሲነፈግ ያበሽቃል። ትልቅ ሀብት መፍጠር የሚችል ነገር ተይዞ እያለ እንደሌለ ሲኮን ግራ ያጋባል። ዛሬ በአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የቆዳና ቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል ለጉብኝት በሄድን ሰዓት ባስተዋልኩት ነገር የተሰማኝን ልበል። የቆዳና ሌጦ ነገር ሀገራችን ከሰባት አመት በፊት እንኳ እንደነበረችበት ጊዜ ከቡና ቀጥሎ የምትተማመንበት የውጪ ምንዛሪ አምጪ እየሆነ አይደለም። ፋብሪካዎች ኦና እየሆኑ ነው፣ አንዳንዶቹ ተዘግተዋል፣ሊለበሱ የሚገባቸው ሌጦዎች ማጌጫ እና መዘነጫ ከመሆን ይልቅ በእየመንገዱ አፍንጫችንን ይዘንባቸው እናልፋለን። የሚጣል ተረፈ ምርት(ቆሻሻ) እየሆኑ ነው። በርግጥ ለዚህ ምክንያቱ አለምአቀፍም ሀገር ተኮርም ተደማምሮ ቢሆን የማያበሽቅ ግን አይደለም! ቢሰራበት የስራ እድል፣ገንዘብ እና ሀብት የሚሆን ነገር ቆሻሻ ሆኖ የማናይበት ዘመንን እመኛለሁ(ኢንሻ ኣላህ) ሌላው እና የገረመኝ፤ በአለም የቅንጦት ፋሽን ገበያ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚይዘው የአዞ ቆዳ የኤክስፖርት መረቡ ከተበጠሰ 15 አመታትን መሻገሩ ነው። የአዞ ቆዳ ምርትን የሚሰጠው አየርባምንጭ አዞ እርባታ ማዕከል ቅርቤ እንደመሆኑ ይህንን ያክል ጊዜ ምርቱ ገበያ ውስጥ አለመኖሩን ሳውቅ አዝኛለሁ።(አይቼዋለኋ!) የአርባምንጭ አዞ እርባታ ማዕከል እስከ 20,000 አዞ መያዝ የሚችሉ ኩሬዎች ሲኖሩት በአመት 3000 የአዞ ቆዳ ለኤክስፖርት ገባያ ዝግጁ ማድረግ ይችላል።(ይሄ እንግዲ ሁሉ ነገር ከተመቻቸለት ነው) አንድ ሴንቲሜትር (1cm) የአዞ ቆዳ ውስጠኛው ክፍል እስከ 5$ ይሸጣል። አንድ አዞ ደግሞ 50cm ድረስ የሚረዝም ቆዳ ሊወጣው ይችላል(250$) እንግዲህ ለ15 ዓመት አንድም አልሸጥንም። መረጃዎች ሳስስ እንደዋና ምክንያት ሆኖ ያገኘሁት የገበያ ትስስር ማጣት እና የገበያ መቀዛቀዝ ነው። ይህ የሚያሳየው ማዕከሉ የገበያ ትስስሩ ቢጠናከርለት እና በጥሩ ሁኔታ ቢተዋወቅ መቸብቸብ ይቻላል(Dear Diaspora think about it!) ጥራቱ ላይ አድምተን ብንሰራ ደግሞ! አጀብ! ከዚህ ጋር በተያያዘ ቦታውን ለመጎብኘት የሚመጡ የቻይና አልፎ አልፎ የጀርመን ጎብኚዎች ስጋውን አስበልተው እንደሚወስዱ እና ለምግብነት እንደሚያውሉት አንድ የቦታው ባለሞያ ሲያወራ አስታውሳለሁ። የአዞ ስጋ በጠቀስኳቸው ሀገራት ተወዳጅ መብል ነው። ስለዚህ ይህ ማዕከል ወደነዚህ ሀገራት ስጋ ኤክስፖርት ማድር የሚችልበት መንገድ ቢታሰብበትስ??? POV: እያሉ እንደሌሉ እየጠቀሙ እንደ ቆሻሻ በምንተዋቸው ነገሮች ላይ እናተኩር። ችላ ባልናቸው በጣልናቸው ነገሮች ውስጥ እልፍ ሀብት አለ!
Hashtags
ታትሟል ሴፕቴ 10
#HaSab #Fishery የምስራቅ አፍሪካ የወሃ ማማ ላይ አሳ እንደልብ አይበላም! እጅግ አሳዛኝ እውነት ነው።ሀገራችን ኢትዮጵያ 13,637 sqkm የሚሆነው ምድሯ በወሃ ተሸፍኖ 51 ሺ ቶን በላይ አሳ በአመት የማምረት አቅም እያላት የምታመርታው እዚህ ግባ የማይባል ነው። በከተሞች አሳ መብላት የቅንጦት ነገር ነው፣ ሀይቅ አልያም ጥልልቅ ወንዞች በሌለባቸው አከባቢዎች አሳ ከመአድ ዝርዝር ውስጥ የለም። እንዲህም ሆኖ ከተጠመደ በኋላ በሚያጋትም ብክነት፣ የመሠረተ ልማት ያለመሟላት እና ትራንስፖርት ችግር ፣የአየር ንብረት ለውጥ እና ሌሎች ችግሮች ምክንያት ጠግበን ያላጣጣምነውን የአሳ ሀብት እያጣን ነው። እየተመናመነ ራሳቸውን ያልተኩ ትንንሽ አሶች እየተጠመዱ ቀጣይነት ያለው ሀብት እንዳይኖረን እየሆንን ነው። ከዚህ በፊት የታቀዱም የተሞከሩም የአሳ ሀብታችንን እንድንጠቀም የሚያደርጉ ስራዎች ሊበረታቱ ይገባል፣ በአሳ ዝርያዎቻችን የሀብት መጠናችን እና የአመጋገብ ስርዓታችን ጥናቶች በበቂ መንገድ ቢደረጉ ቀላል ፋይዳ አይኖረውም። የፈጠራ ስራዎች ተስፋፍተው በዘርፉ ቢሰማሩ አስቡት! አምራቾች ድፈሩ! Aquaculture ሀገራችን ውስጥ መስፋፋት አለበት። ሰዎች ከሀይቅ እና ወንዞቻችን በተጨማሪ በሰውሰራሽ ገንዶዎች አሳን ማምረት እና ማከፋፈል ይችላሉ። የሚችለውም የሚመለከተውም በተቀናጀ ሁኔታ ከሰራ በምስራቅ አፍሪካ የወሃ ማማ አሳ እንደልብ ይበላል። Yared E. (3rd year DVM student at AAU-CVMA)
#HaSab #Animalhealth መኝታ ብቻ እስኪለይህ አብረሃት የምትውል ግልገል ከነ እናቷ ተሽጠው ወደ ገዥው አልሄድም ብላ ወዳንተ ዞራ ስትጮህ አልቅሰሃል? ጥጃ በስምህ ተገዝቶልህ ስታድግ ወተቷ ያንተ ነው ተብለሃል? ለውሻህ ስጋ ለድመትህ ሳምባ ለማምጣት በለሊት ቄራ ድረስ ሄደሃል? በምሽት ሁሉም መግባታቸውን ቆጥረህ አስገብተህ ጠዋት በራቸውን ከፍተህ ከከፍታው ጎጇቸው እየበረሩ ሲወርዱ ጥሬ ሰጥተህ እንቁላል የሚሰጡህን ዶሮዎች ተንከባክበሃል? ከእነዚህ ቢያንስ አንዱን ሳያደርግ ያደገ መኖሩን እጠራጠራለሁ። በልጅነታችን እንኳን ለሰው ለእንሰሳም እጅግ ስስ ነን። ፍቅራችን ልዩ ነው። ይህንን የልጅነት ስስት ጣዕም አሁን እያገኘሁት ነው። በእንሰሳት ህክምና ኮሌጅ ውስጥ ስለ እንሰሳት ጤና አጠናለሁ። ስቃያቸው ምንድነው፣ እንዴት ህመማቸውን ልረዳ እችላለሁ፣ ተፈጥሯቸው እንዴት ያለ ነው፣ ከሰዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት እንዴት ያለ ነው ስል አስባለሁ። በፊት በፊት በውስጤ በለው ስሜት አሁን ደግሞ ተፈጥሯቸውን ይበልጥ በመረዳት ቅርባቸው ሁኛለሁ(ታድያለሁ)። ህመሙን ማስረጃ አንደበት የሌለውን ፍጡር ከመረዳት በላይ ምን አለ? በሀገራችን እንስሳ ማርባት የቅንጦት ጉዳይ አይደለም። ሁለት በሬዎች ከአባቶቻችን ጋር መግበው አስተምረው ያበቁን ነን። አንዲት ላም ቤተሰብ ስታስተዳድር የወተት ገቢ ምርቷ የቤተሰብ ቀዳዳ ሲሸፍን ተመልክቻለሁ። አንድ አህያ እውነት አንድ ብቻ ነች? ስንት ሸክማችንን አቅልላለች? በሀገሬ እልፍ ህዝብ አርብቶ አደር ነው። ህልውናው፣ የልጆቹ ተስፋ፣ በማህበረሰቡ ያለው ደረጃ እጁ ላይ ባለው እንስሳ ሀብት የተወሰነ ነው። የእነዚህ እንስሳት ጤና መታወክ እና ምርት መቀነስ የቤቱን መሠረት ያናጋዋል። ይህ መሠረት እንዳይናጋ ነው መማሬ። የእንስሳቱን ጤና መጠበቅ ጤናማ አመጋገብ እንዲኖረን ያደርግ የለ? ለወገን ጤና ነው መማሬ። ሀገሬ የምትኮራበት ኤክስፖርት የምታደርገው ሌጦ አላት። አለም ከኢትዮጵያ በተገኘ ቆዳ የተሰራ ጫማ ሲሉት ተሽቀዳድሞ ይገዛል። በእንክብካቤ ያደጉ የቆዳ ጤናቸው የተጠበቀ እንስሳት ሲኖሩን ደግሞ አስቡት። የእንስሳት ጤና ጥቅሙ እጅግ ብዙ ነው። Yared Ermias Second Year Student at AAU-CVMA
Hashtags
ታትሟል ሴፕቴ 10
#HaSab #Veteducation ለ12ተኞች አድርሱልኝ🙏 በቅድምያ ሀገራችን ያለችበት ነባራዊ ሁኔታ በትምህርታችሁ ላይ ያደረሰውን ጫና ተቋቅማችሁ የሚያስደንቅ ውጤት በጥረታችሁ ላመጣችሁ ተማሪዎች አድናቆት እና አክብሮቴ ይድረስ።(በናንተ የወደፊቷን ኢትዮጵያ መልካም እንድትሆን እመኛለሁ) በተለይ ባለፉት ሦስት እና አራት አመታት ውስጥ የ12ተኛ ክፍል ፈተና ማለፍ አይደለም መፈተን በራሱ ብዙ ችግሮች ያሉበት ነው።(እንክርዳድ የበዛበት እህል ሆኗል)። በርግጠኝነት ቀለሜ ሆነው ዝግጅት በማድረግ ላይ ሳሉ በተደረጉ ብርታትንና ሞራልን የሚያደክሙ ውሳኔዎች የተሰበሩ ውጤታቸው እንደምኞታቸው ያልሆነላቸው የነገ ሀገር ተስፋዎች ይኖራሉ(እናንት ጠንካሮች ሆይ ተነሱ አቧራችሁን አራግፋችሁ ለእንደገና ሩጫ ራሳችሁን ኣበርቱ) EUEE እንደ ድሮው ኣይደለም።ጭራሽ ምንም ዝግጅት ሳያደርጉ ትምህርት ሚንስቴር አይቶ አይኔን ግንባር ያድርገው አላየሁም እያለ እልል ብለው በተሰረቁ ፈተናዎች ያለፉ ተማሪዎች እንዳሉ ሀቅ ነው። ለእነዚህም ሆነ ለሌሎች ተማሪዎች ንቁ! ዩኒቨርስቲ በተለይ የመጀመርያ አመት የመጀመርያ ሴሚስተር የሚከተለው ነው የሚል እንዳለፈበት ተማሪ መጠነኛ ሀሳቤ ይድረስ.... ውጤታችሁን እንደመመልከታችሁ ከወዲሁ ለሚጠብቃችሁ ኮርስ በትበት ብትሉ አሪፍ ነው። የፍሬሽ ማን ኮርሶች ከጥቂቶቹ በቀር ከ11 እና 12ተኛ ክፍል ትምህርት ጋር ያው ናቸው።(ለfinal exterme series መጽሐፍትን ነው ያነበብነው)። ችግሩ ያካልቧችኋል። አርፍዳችሁ እንደመግባታችሁ የምትማሩት ለመጨረስ እንጂ ለመረዳትም አይመስልም...ቀድማችሁ ዝግጅት አድርጋችሁ ብትገቡ ግን ቀለል ይልላችኋል። ጫናውን አሁን ባላችሁ ትርፍ ግዜ ትቀንሱታላችሁ።(እንዲያ አድርገው የገቡ ተማሪዎች በብዙ ነበር ያተረፉት)። የትምህርት መርጃ መጽሐፍት እና ስለ ኮርሶች ያለውን ሁሉMuja MercuryyyATC tube ላይ አስቀምጦላችኋል(ይመችህ ኣባቴ) ሁሉም ነገር ግዚያችንን ይፈልጋል። ሁሉም ቢተገብርቱት ጥሩ ትሩፋት ኣለው። በተለይ አስታውሳለሁ ዩኒቨርሲቲ ስገባ ኣደርጋቸዋለሁ የምላቸው መልካም ነገሮች ሁሉ ግርርር ብለው መጥተውብኝ የቱን ላስቀድም የሚለው ነገር በጣም ግራ ኣጋብቶኝ ነበር። የፍሬሽ ማን ኮርስ ደግሞ ግዜ አይሰጥም። ቀጣይ የምትመርጡት ፊልድ አሁን ባመጣችሁት ውጤት እና በመጀመርያ ሴሚስተር ባመጣችሁት(ለአንዳንዱ ሙሉ የመጀመርያ አመት) ውጤት ላይ የተመሠረተ ነው። ታድያ ግዜያችሁን በይበልጥ የነገ ጉዟችሁን በሚወስነው ችከላ ላይ ማድረግ ሸግዬ ነው(ያራድዬ ልጅ የሚያደርገው እንደዛ ነው) ዩኒቨርሲቲ ከመግባታችሁ በፊት ስለ ግቢዎች ወይም ፊልድ ከመምረጣችሁ በፊት ስለ ፊልዶች የሚነዙ ቀልዶች እንዳያስቷችሁ ተጠንቀቁ። ብዙዎቹ ሰዎች እንደሚሉት አይደለም። በጭፍን የምትጠሏቸውን ግቢዎች እና ፊልዶች አጢኗቸው። ለተራ ቀልዶች እጅ አትስጡ። በተለይ እንደግል ያለኝ ምክር የፊልድ መረጣችሁ በፍላጎትና ችሎታችሁ ይሁን የሚል ነው(ሸግዬ ውጤት ካላችሁ የፈለጋችሁበት መግባት ኣያሳስብም) "ያበላል?" የሚለው ጥያቄ interest በሌላችሁ ፊልድ ላይ እንደመግብያ ሰበብ ባትጠቀሙ መልካም ነው። ምክንያቱም የሚያጠግብ እንጀራ ለመብላት መጀመርያ እንጀራ መውደድ ያሻል!! Lets talk vet!💙 Veterinary medicine በሀገራችን ባሉ በአስራ የሚቆጠሩ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል። እውነት ለመናገር DVM እንደደረሰኝ ባወኩ ግዜ እጅግ ትልቅ ሀዘን እና ተስፋ መቁረጥ ነበር የተሰማኝ። የደረሰኝን የሰሙ ሁሉ ፊታቸው ጨፍጋጋ ነበር(ከጥቂቶቹ በቀር)። ገብቼ ልየው ካልሆነ እቀይራለሁ በሚል መንፈስ ነበር የገባሁት። ነገር ግን ጥቂት እንደተማርኩ የገባኝ እጅግ ድንቅ ሳይንስ(የልብ የሚያደርስ) እና ሰፊ የስራ መስክ ያለው ሞያ መሆኑን ነው። ከምነግራችሁ በላይ አድማሰ ሰፊ ነው። እንደኔ ለህክምና ሞያ ጥልቅ ፍቅርና ጉጉት ያላችሁ ተማሪዎች ስለ እንስሳት ህክምናም ብታስቡና በቂ ጥናት ብታደርጉ ባይ ነኝ። ለሀገርም ለራስም የሚበጅ ነገር በዚህ አለ(እስቲ The Blue Vetን ሾፍ አድርጓት) በቀረውስ ያሰባችሁት የሚሰምርበት የትምህርት ዘመን ከፊታችሁ እንዲመጣ እመኛለሁ። ሀገራችን ሰላም ሁና ሁሉም ወጣት የሚመኘው እየተማረ እንዲኖር ምኞቴ ነው። መልካም እድል! ሻሎም! Yared Ermiyas Second year student, AAU-CVMA (DVM)
Hashtags
ታትሟል ሴፕቴ 10
ታትሟል ሴፕቴ 5
Channel photo updated