TGTGInsighttelegram intelligenceLIVE / telegram public index
ወደ ቻናሎች ዝርዝር ተመለስ
#HaSab avatar

TGINSIGHT CHAT

#HaSab

@Hasab_2016

Education

#HaSab ያለማል ፤ #HaSab ያጠፋል! አልሚ ሀሳቦች በዚህ አሉ! @yared2774

ደምበኞች77የአሁን ደምበኞች
የተከታተሉ ልጥፎች169የተዘረዘሩ ልጥፎች ቁጥር
የቅርብ ጊዜ ደረሻ3,937የቅርብ ጊዜ ዕይታዎች ድምር
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች

የቅርብ ጊዜ ልጥፎች

ገጽ 10 ከ 15 · 169 ልጥፎች

ታትሟል ሜይ 23

Handover 🤝 keynote from former one health Club secretary. As I reflect on my tenure as the Secretary of the Addis Ababa University One Health Club for the year 2016 E.C., I am filled with gratitude for the enriching experiences and valuable lessons learned. This past year has been truly transformative as I delved into the intricacies of One Health, deepening my understanding of its implementation within our community. I had the privilege of connecting with esteemed experts and academicians who share a common concern for the interlinked health of humans, animals, and the environment, fostering a network of like-minded individuals dedicated to this cause. Assuming the role of Secretary has been a catalyst for personal growth, allowing me to hone my skills in document preparation, promotional writing, poster design, and event concept development. It is through shouldering responsibilities that we acquire practical knowledge and expertise, and I am grateful for the platform this position provided for my professional development. Central to our endeavors has been the spirit of teamwork, inherent in the essence of the One Health concept itself. I commend my esteemed colleagues, President Lemi Erana, Finance Officer Mieraf Tewelde, and Vice President Tamirat Go, for their unwavering dedication and resilience in overcoming challenges, which has forged us into a cohesive and formidable team. Over the course of this year, we have achieved significant milestones, including the successful organization of three online webinars, knowledge-sharing initiatives with universities, and a fruitful collaboration with the Kyeema Foundation to raise awareness about One Health. As we pass the baton to our successors this week, I extend my heartfelt best wishes to them. We stand ready to offer our support and share our experiences to facilitate a seamless transition. I express my profound gratitude to Addis Ababa University College of Veterinary Medicine and Agriculture, my dedicated team members, and the generous support of the Kyeema Foundation. A special acknowledgment goes out to Dr. Tilaye, Dr. Yimesgen, Mulusew (from Jimma University), Abebe, Layla (from Haremaya University), Dr. Bruk (from Gonder University), and Dr. Tadiyos (Kyeema Foundation), Dr. Hanna (SPANA Ethiopia) Sewagegnehu (from UoG) for their invaluable guidance and assistance when needed. Together, we can continue to make a meaningful impact in advancing the principles of One Health. Thank you. Yared E.

878 views

ታትሟል ሜይ 23

721 views

ታትሟል ሜይ 17

#Animals_Fact Parrots have a unique ability to mimic sounds, including human speech. They have a specialized vocal organ called the syrinx, which allows them to produce a wide range of sounds. Parrots learn to speak by listening to and mimicking the sounds around them, including human speech. They are able to mimic words, phrases, and even sounds like ringing phones or barking dogs. Training a parrot to speak involves repetition and positive reinforcement. By consistently repeating words or phrases in a clear and distinct manner, and rewarding the parrot with treats or praise when they mimic the sounds correctly, you can encourage them to learn to speak. It is important to be patient and consistent with training, as not all parrots will be able to speak or mimic sounds.

366 views

ታትሟል ሜይ 13

Dosis Sola facit Venenum ከ500 አመት በፊት አጀብ ያስባለ ጽንሰ ሀሳብ ነው። ምክንያቱም ከጥንት ጀምሮ በገፍ የተሰጠ ጥሩ ነገርን የመሠለ ምንም የለም የሚል እሳቤ አለ። ከላይ የጠቀስኩት ጽንሰ ሀሳብ ይህንን የናደ ይመስላል። የእንግሊዝኛ አቻው "The Dose makes the poison" ማለት ነው። በጤና ዘርፍ የተማራችሁ ወይንም Toxicology የማጥናት እድል ያገኛችሁ በደንብ ታውቁታላችሁ። የToxicology ሀሁ ነው። ወደ አማርኛ ስንተረጉመው 'መርዙ የወሰድከው ነገር ሳይሆን የወሰድክበት መጠን ነው።' እንደማለት ነው። ቆጣ ያለ የአባት ምክር አድርገን ከገለጽነው ደግሞ በሁለት ቃል: 'ልክህን እወቅ!' የሃሳቡ ባለቤት Paracelsus ይባላል። ሙሉ ስሙ የጀማሪ ግጥም ነው የሚመስለው። phillippus Aureolous Theophrastus Bombustus Von Hoheneim. ያው ቤት ግን አልመታም። ሰውዬው በዘመኑ የነበረው የትምህርት ስርአት ስልችት ያለው አፈንጋጭ ነበር። ትኩረቱን በሳቡት ነገሮች ላይ እስከ ጥግ አንብቧል፣ ተመራምሯል ፣ የተሻለ እውቀት ፍለጋ ከተወለደባት ሲውዘርላድ ተነስቶ አውሮፓን ዞሯል። ዋና ትኩረቶቹ ህክምና ፣ ኬሚስትሪ ፣ ፍልስፍና እና ስነ ከዋክብት ነበሩ። በእነዚህ ዘርፎች ብዙ የተናገራቸው ግራ አጋቢም እውቀት ገንቢም ነገሮች አሉ። ከእነዚህ መካከል አሁን እያወራንበት ያለው ጽንሰ ሃሳብ አንዱ ነው። The Father of Toxicology አስብሎታል። በህክምናው ዘርፍ Groundbreaking የምንለው አይነት ጽንሰ ሃሳብ ነውና። ሀሳቡ በዋናነት ለሁለት ነገር ትልቅ ጥቅም የሰጠ ነው። የመጀመርያው:- it described the phenomenon in which poisonous substances can be medicinal in small dosage. መጠን ከሆነ መርዝን መርዝ ያደረገው መርዝም መድሃኒት ሊሆን ይችላል እንደማለት ነው። ለምሳሌ hydrogen peroxideን እንመልከት የጥርስ ሳሙናችን ውስጥ የሚገኝ Chemical ነው። አፋችን ውስጥ ያሉ ባክቴሪያዎችን ለመግደል ይጠቅማል። ይህ ኬምካል ግን መጠኑ ከፍ ብሎ ወደ ሰውነት ሲገባ መርዛማ ነው። ሊገድልም ይችላል። ልኩን እስካወቅን ግን 'አያሳስብም' ሌላኛው የዚህ ጽንሰ ሃሳብ ትልቅ ጥቅም:- its a base for public health standard , which specify maximum concentration in food , public drinking water, and the environment. ለምሳሌ ከዚህ በፊት ስለ አፍላቶክሲን ጽፌላችሁ ነበር። አፍላቶክሲን ለካንሰር አጋላጭ ነው። ይህ መርዛማ ኬሚካል በወተት አልያም በእንስሳት መኖ ላይ ሊገኝበት የማይገባ መጠን አለ። ከዛ መጠን ካለፈ አደጋ አለው። መጠኑን እስካልተሻገረ ግን ችግር የለውም። እንደ እውነቱ ከሆነ 'ዜሮ የአፍላቶክሲን መጠን ያለበት ምግብ' ለማለት ይቸግራል። መጠኑን እስካወቅን ግን 'አያሳስብም' አኔ ደግሞ አንድ ልጨምር። ፍካሬያዊ ፍቺ በሉት። የAI ነገር። አሁን አሁን በብዙ ተማሪዎች ጥቅም ላይ ሲውል እንደማየቴ ያሳስበኝ ጀመሯል። ያሳሰበኝ መጠቀሙ አይደለም። እንደ እውነቱ ከሆነ እኔም ወድጄ የምጠቀመው እና የማደንቀው ፈጠራ ነው። ችግሬ ከመጠኑ ነው። የምንጠቀምበት መጠን የፈጠራ ችሎታችንን እንዳያቀጭጨው እፈራለሁ። ጭንቅላታችን ጉልበት ማባከን የሚወድ አይደለም። ቶሎ እፎይ ማለት ይፈልጋል። በቶሎ በሚገኝ እፎይታ አንዳንዴ በመሥራት ሂደት ውስጥ የምናገኛቸውን 'ኢዮሪካ' የሚያስብሉ ሀሳቦች ልናጣ እንችላለን። ምንም ቴክኖሎጂ አጀብ የሚያስብልበት ዘመን ላይ ብንሆን አሁንም አቧራ በለበሱ የላይብረሪ መጽሐፍት ውስጥ እልፍ እውቀቶች፤ ያልተጨመቁ እንብበን ስንጨርስ በሚገርም ሁኔታ ጨምቆ የመረዳት ክህሎት የሚሰጡ ሀሳቦችን እናገኛለን። ምን ጊዜ ቢከንፍ እኔ እና ቤቴ ግን ቁጭ ብሎ ማሰላሰል የሚበጅበት ጊዜም አለ ብለን እናምናለን። ስለዚህ በፍጥነት መጓዝን እና ፈጠራ የታከለበት ማዝገምን ማመጣጠን ከኛ የሚጠበቅ ነው። መጠኑን እስካወቅን ግን 'አያሳስብም' Bona nocte!

1,200 views

ታትሟል ሜይ 13

312 views

ታትሟል ሜይ 12

62 views

ታትሟል ሜይ 12

ሌላው ከሚመታህ እኔ ልምታህ! አንድ ቀን ጂሙ የሰውነት ቅርጻቸውን ለማስተካከል በሚለፉ ወጣቶች በተሞላበት ሞ! ወደ ውስጥ ገባ። ሞ ማነው እንዳትለኝ! ግራ ከገባህ የትናንት ፖስቴን ግባ እና ተመልከት። "ሰውነት ያለ ቴክኒክ ምን ያደርጋል?" ሁላችንም ዞር ብለን ተመለከትነው። ሞ ስፖርት የሰውነት ቅርጽ ብቻ ሳይሆን የቴክኒክ እውቀቶችም ሊኖርት እንደሚገባ ያምናል። ስፖርት ሰርቶ ሰውነቱ ደንዳና የሆነ ነገር ግን ቢሰነዘር መከላከል የማይችል ሲሰረቅ ለነፍሴ ብሎ ቆሞ የሚያይ እንዲኖር አይፈልግም። ጥሩ የቦክስ ውድድር ልምድ አለው። ከተማዋን ወክሎ አሸንፈቀል። ያለውን ልምድ በነፃ ሊያካፍለን በነፃ መሰረታዊ የቦክስ ቴክኒኮችን ሊያሰለጥነን መወሰኑን እና እንድንመዘገብ ነግሮን ወጣ። ደስ ብሎን ተመዘገብን። አንተ! ቦክስ የዋዛ ስፖርት እንዳይመስልህ። የሰውነት ጥንካሬ እና ቅልጥፍናን፣ የአእምሮ ፈጣን መላሽነት እና አስተውሎትን እንዲሁንም በተገጣሚው እንቅስቃሴ መሰረት ፈጣን ብልሃቶችን መዘየድን ይጠይቃል። የምንግዜም ምርጥ ከሚባሉት ስፖርተኞች መካከል የሚመደበው አሁን ጓንት የሰቀለው አሜሪካዊው professional Boxer Floyd Mayweater Jr. "Boxing is not about your feeling. Its about performance" ይላል። ይህም Mindsetቱ የተገነባባበት መሠረት እንደሆነ ይናገራል። Mayweater በመከላከል ብቃቱ ፣ ፍጥነቱ እና ከተጋጣሚው ለሚደርሱት ስንዘራዎች ፈጣን ምላሾች(Counterpunching) የሚታወቅ ሲሆን ይህ ሊገነባ የሚቻለው ከውጪ በሚመጣ ጊዚያዊ Motivation እና ሞራል በላይ በልምምድ፣ ዲሲፕሊን እና በቂ ዝግጅት መሆኑን በጽኑ ያምናል። ወደ ቀድሞ ነገራችን ስንመለስ ይሄ ሁሉ የገባኝ በመጀመርያው ቀን ነው። የተጨበጠ ቡጢ ለመሰንዘር ብቻ ሳይሆን አይን እና አገጭን ለመከላከል እንደሚጠቅም መች አውቄ? ቡጢ ለመሰንዘር የእግር እንቅስቃሴ ሳይቀር ወሳኝ እንደሆነ መች አስቤ? ወላ ለቦክስ ትንፋሽ እንደሚያስፈልግ ታውቃለህ? አንድ ሁለት ቴክኒኮችን ስሜታዊ ሆነህ እንደሞከርክ፤ ሳንባህ ይሄ ልጅ አላኖረኝም ካልወጣሁ ይላል። ልብህ የአውሊያ ቤት ድቢ ያስንቃል። እጅህ ይከዳሃል። ቢሆንም ቢሆንም ደስ ይላል። ሞ! ታድያ በእጁ ላይ ባጠለቀው ጓንት የነገረንን ቴክኒክ እንድንሞክር ያደርጋል። ትኩረታችን መሠንዘር ላይ ሆኖ መከላከል ሲዘናጋን በክፍተቷ ተጠቅሞ ይመታናል። ታድያ ከዚህች ምት በኋላ ሁሌ የሚናገራት ቃል አለች። "ዋ! ሸፍነህ ሰንዝር። እመታሃለው! ሌላው ከሚመታህ እኔው እዚህ ብመታህ ይሻላል"😂 ይህቺ አባባሉ ደስ ትለኛለች! አሁን አሁን ብዙዎቻችን የምንፈልገው ከሚነቅፈን ይልቅ የሚያሞግሰንን፣ ስራችን ላይ አሉታዊ አስተያየት ካለው ይልቅ በጭፍን የሚያደንቀንን እየሆነ የመጣ ይመስለኛል። በ 'አንቂዎቻችን' የምናደርገው ልክ እንዳልሆነ ከሚነግሩን ሰዎች እንድንርቅ ተመክረናል። በአንድ በኩል ምንም ብንሆን ግድ የማይሰጣቸው ሰዎች አሉ። ወዲህ ደግሞ ክፍተታችንን ሲያዩ እንድንሸፍነው የሚመቱን እንደ ሞ! ያሉ ሰዎች አሉ። ግሳጼ ደስ የሚል ስሜትን የሚፈጥር ነገር አይደለም። እኚህ ሰዎች ሊሰብሩን ሳይሆን ስለ ስብራት እንዲገባን የሚጎስሙን ናቸው። እድገታችንን የሚሹ። ያለን ክፍተት ቡጢ የምንቀምስበት እንዲሆን የማይፈቅዱ። እነሱ በተመቱበት እንዳንወድቅ የሚጥሩ። ግሳጼያቸው፣ ቁጣቸው ለብርታት የሆነ። በህይወታችን ውስጥ እንዲህ ያሉ ሰዎች ያስፈልጉናል። በሰዎች ህይወት ውስጥ እንዲህ ያለ ሰው መሆን ይገባናል። ሰላምህ ይብዛ ሞ! ቸር ያቆየን

63 views

ታትሟል ሜይ 10

ሞ! ጂም የሚሄድ የCVMA ተማሪ ስለማን እንደጻፍኩ ይገባዋል😅🔥 በደዘ ወጣቶች ስለሚወደደው እና እጅግ ስለሚከበረው ሰው ልንገራችሁ። ደዘ ቢሾፍቱ ነች። የሚወዷት የቀድሞ መጠርያዋን አሳጥረው ደዘ አልያም ቢሼ እያሉ አፋቸው ላይ ያጣፍጧታል። ምርጥዬ ከተማ ነች። የሰባት ሀይቆች እመቤት፣ የኤረር ተራራ ግርጌ፣ ከዋሽንት የሚፈልቅ የሚመስለው ነፋሷ ነፍስን የሚዳስስ ነፍስ የሆነች ከተማ። ሞ! የስፖርት ሰው ነው። ከተማዋን ያስጠራ የቦክስ ተወዳዳሪ። ስፖርት እጅግ በጣም ይወዳል። ልጅነቱ ከጀግኖች የሀገር ወታደሮች ጋር ያሳለፈ በመሆኑ ስፖርትን እና ዲሲፕሊንን አብሮ ይዟል። ካገኘሁት ጀምሮ ትንሽ ትልቁን ያከብራል። ትንሽ ትልቁ ያከብረዋል። ከተማ ውስጥ "ብርት መግፋት ያስጀመረኝ ሞ ነው" ፣ "ኳስ መጫወት የወደድኩት ሸማኔ ሜዳ ነው "የማይል ወጣት መኖሩን እንጃ። የከተማዋን ልዩ ትዝታዎች አንጣላ ከያዘችው ሸማኔ ሜዳ ጀርባ ሞ ጂም አለችው። እዛች ጂም ውስጥ የሚፈረጥመው ጡንቻ ብቻ አይደለም። ስብዕና ይገነባል፣ ታላቅን ማክበር ባህሪ ይሆናል፣ ታናሽን ማስተማር ባህል ነው። ያቺ ጂም አክብሮ የሚከበር ወጣት መፍለቅያ ነች። ይህ የሆነው ደግሞ በ ሞ! ነው። ማሞ። ማሞ ከድር። ለደብረዘይት ወጣትና ስፖርት ትልቅ ዋጋ የከፈለ ጀግና ሰው! ሞ! አቀርቅረህ እንድትራመድ አይፈልግም። ቀና በል ወንድ ልጅ ነህ ይልሃል። ሞ ቀጥነህ አልያም ቦርጫም ሆነህ ማየት አይፈልግም። መንገድ ላይ እንዲያ ሆነህ ቢያይህ ነገ ቀጥ ብለህ ጂም ና ይልሃል። ሞ! ስፖርት ትጥቅ ሳትለብስ ጂም ስትመጣ ማየት አይፈልግም። ለስፖርት ክብር ይኑርህ ይልሃል። ሞ! ከፍያለሁ ብለህ ባሻህ ሰአት መጥተህ ባሻህ ሰአት ጂም እንድትቀር አፈቅድልህም። ዲስፕሊን ከሌለህ ምን ጥቅም ይልሃል።ስትሳሳት ያርምሃል፣ ስፖርት ሰራሁ ብለህ ሰፈር ብትበጠብጥ ያስጠነቅቅሃል። ብቸኛ ከሆንክ ጓደኛ ይሰጥሃል።ይህን ሁሉ ሲያደርግ ደስ እያለው ነው። የሚቀመጥባት ቦታ አለች። ገና ወደ ግቢው ስትገባ ፊትለፊት ታየዋለህ። ግርማ ሞገስ አለው። ሰላምታ ይሰጥሃል። የጁምኣ ቀን ከሆነ ነጭ ጀለቢያውን ለብሶ ድምቅ ብሎ ይቀመጣል። ከውጪ ሆነው የሚሰሩትን እየተመለከተ ያርማል። በቃ መኖሩ ብቻ ድባብ የሆነ ሰው ነው። ወደዛች ጂም በሄዱኩባቸው ጊዜያት ሁሉ ስለ Social wealth አሰላስያለሁ። አንዳንድ ሰዎች ሀብታቸው ሰው ነው። በለ ግዙፍ ስብዕና ናቸው። የሚወደዱት ስለሚወዱ ነው። የሚከበሩት ስለሚያከብሩ ነው። የሚፈሩት ከመውደድ በመነጨ ፍርሃት ነው። Social wealth ካሉት አምዶች መካከል ሦስቱ Strong social network, High level of social influence and Supportive relationship ናቸው። እነሲህ አምዶች ሰው ሆነው በማሞ ከድር ተገልጠዋል። ሞ ያለው ሀብት ብዙ መሪዎች ቢኖራቸው የተመኘት ነገር ግን ያልታደሉት ነው። ሰሞኑ ከዚህ ሰው የተማርኳቸው ነገሮች ጭንቅላቴ ውስጥ ተመላለሱ እና ልጽፍ ወደድኩ። ቆይ አንድ የማጋራችሁ ጽሑፍ አለኝ! እስከዛ የሞን ታሪክ በዚህ ቃለ ምልልስ ከአንደበቱ አድምጡልኝ🙏 https://youtu.be/8NRm6rF5B68?si=1dA_QYQmjO5qlavk

58 views

ታትሟል ሜይ 10

62 views

ታትሟል ሜይ 5

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2016ዓ.ም የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በአሉን የሰላም ፣ የፍቅር፣ የደስታ ያደርግልን ዘንድ Campus Voice ይመኛል! መልካም በዓል!💛

75 views

ታትሟል ኤፕሪ 27

Happy World Veterinary Day 2024💙 #WVD2024#worldvetday#worldveterinaryday@worldvet@worldvetAssoc World Veterinary Association (WVA) World Organisation for Animal Health The Blue Vet AFROHUN Ethiopia Ethiopian Veterinary Association (EVA)

64 views

ታትሟል ኤፕሪ 24

ትዝ ብሎኝ እኮ ነው! ቡሄን በእንግሊዝኛ ለህንዳውያን ለማስረዳት የሞከርኩ ሰው ነኝ። አሁን ሳስበው ሙከራው ውርጭን በካኒቴራ በረሃን በብርድ ልብስ ለመጓዝ የመድፈር ያክል ነበር። አስቡት ቡሄን ያክል ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚከበር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ትውፊት የህንድ እውቅያኖስን ተሻግሬ የተለያዩ ቋንቋዎች ለሚነገሩባት ህንድ ነዋሪ ሳብራራ። ዝም ብላችሁ አስቡት.... ወዲህ በአማረኛ እያሰበ ወደ እንግሊዝኛ ተርጉሞ የሚያወራ የኔ "ሜዱላ" አለ። ወዲያ የኢትዮጵያ ባህል በወሬ ካልሆነ አይተው የማያውቁ በእንግሊዝኛ ሰምተው ህንድ ውስጥ ካሉ ቋንቋዎች በአንዱ የሚረዱ እነርሱ አሉ። ልገነባ ያሰብኩት ድልድይ ቋንቋን ፣ ባህልን ፣ ስነ ልቦናን እና ሐይማኖትን ተሻግሮ በሀሳብ ተግባብተን ጭንቅላታችንን እንድንነቀንቅ ሊያደርግ የጠነከረ መሆን ይገባዋል። ይህን ድልድይ በጥቂት እውቀት ለመገንባት መሞከር በርግጥ እብደት ይመስላል። ...But we did it በዘነዘና😅 ነገሩ እንዲህ ነው። መቼም ሮትራክትን ታውቃላችሁ?! የሮትራክት ኩሪፍቱ ክበብ አባል ነኝ። በሮትራክት ክለቦች ውስጥ ደግሞ International Relationship የምንለው ነገር አለ። በአጭሩ ሲገለጽ ክለቦች ከሌላ ሀገር አቻዎቻቸው ጋር ልምድ ልውውጥ የሚያደርጉበት እና የጋራ ስራ የሚሰሩበት አይነት ነው።በክለቡ ውስጥ ይህን የሚመራ የራሱ ዳይሬክተር ይኖረዋል። የኛ ዳይሬክተር ሜቲ ትባላለች። ሜቲ ህንድ ሀገር ከሚገኝ ሮትራክት ክለብ ጋር የ online Cultural exchange event ለማዘጋጀት እየተጻጻፈች እንደሆነ ነገረችን። ይበጅሽ "ቲኬ ሜትሪና" አልናት። ሜቲ ኦሮምኛ ቢሆንም ካትሪና የሚባል የህንድ ስም እናውቃለን እና ህንዳዊ ለዛ አስያዝነው። በየስብሰባችን ስለ Eventኡ እንድትነገረን ስንፈልግ "ናማስቴ ሜትሪና ያ ነገር ከምን ደረሰ?" እንል ነበር። ትንሽ ሳቅ ይፈጥራል። ቀኑ ከይደርስ መስሎን! ይህ ሁሉ ሲሆን ባህላችንን የሚያስተዋውቀው ማን እንደሆነ ገና አላወቅንም ነበር። ኸረ ጉዴን አላወኩም ነበር ብል ይቀለኛል! ለማቅረብ ቀናት ሲቀሩን ጉዴ ተነገረኝ። "አንተ ነህ ምታቀርበው" ተባልኩ! በሻሩክ ሞት! አልዋሻችሁም ጨነቀኝ። ወላ ጠበበኝ። ስለማቀርበው ነገር ሳስብ ቀኑ ቶሎ ያልቅብኛል። " 'ራት ሰዓት ላይ አሁን አይደል ምሳ የበላሁት?" እላለሁ። ጠዋት ስነሳ ከምኔው ነጋ እላለሁ። የአንስታይን ሰራተኛ እውነቷን ነው። ስለ ጊዜ ሲጠይቃት ከፍቅረኛዬ ጋር የተቀጣጠርኩ ጊዜ ሰዓቱ ለመድረረስ ዘላለም ነው ፣ ከተገናኘን በኋላ ደግሞ የዘገየውን ሊያካክስ ነው መሠል ሽምጥ ይጋልባል ያለችው። እኔ ቀጠሮዬ ከፍቅረኛዬ ጋር አይደለም። በምን እድሌ! ለኔ ሰአቱ ከጭንቅ ቀኔ ለማድረስ ነው ሽምጥ የጋለበብኝ። በተቻለኝ አቅም ስለ ቡሄ ለማንበብ ከልጅነቴ ለማስታወስ ሞከርኩ። ጭራሽ ለማወቅ በጣርኩ ቁጥር ቡሄ የማላውቀው አንዲስ በዓል ሆኖ ቁጭ አለ። ትውፊቱ ፣ አንድምታው ለኔ በየአመቱ እየጠበኩ ለማከብረው ደነቀኝ። እንደ አዲስ የገረመኝ ነገር ነው እንግዲህ ቋንቋ ቀይሬ ማቀርበው! ሲፈጥረኝ መድረክ ሁሌ አዲስ ይሆንብኛል። የሚያደምጠኝ እንዲሰላች አልፈልግም። የታዳሚው ብዛት ምንም ይሁን ምን ሰአቱን ሰውቶ መገኘቱን አከብራለሁ። ቢቻል ቢቻል ከመድረኩ አዲስ ነገር ማግኘት አለበት። አልያ ደግሞ ከዚህ በፊት የሚያውቃቸው ነገሮች እንኳ በአዲስ እይታ ተቃኝቶ እንዲያገኘው እፈልጋለሁ። በእኔ እምነት የመድረክ ሰው ግብሩ ቡና መሆን ነው። ታዳሚ ንቅት ብሎ ሀሳብ ወደ ምዕናቡ እንዲፈስ ማድረግ። ምንም እንኳ ይህ የonline መድረክ ቢሆንም(ነገር በአይን ይገባል ባይባልለት) ዝግጅቱ የማይሰለች ለዛ እንዲኖረው ፈልግያለሁ። ስለዚህ እንደ መግብያ ህንድ እና ኢትዮጵያን የሚያጋራ ነገር ማውራት ፈለኩ። እኔ እና አንድ የህንድ ወጣት ምን የጋራ ነገር አለን? ምን አይነት ተመሣሣይ ልጅነት ነበረን? አብረን ጭቃ አብክተናል? ቴዘር እነርሱ ጋር ይኖር ይሆን? እሺ መሃረቤን አያችሁ ወይ ተጫውተዋል? ለህንድ ህፃን ከማር ከወተት መጓተት ይሻላል? አሃ! አንድ ነገር አለ! ሻሩክ ካን። ያ የህንዱ የፍቅር ተምሳሌት። Bollywood! በቃ ስለ Bollywood አወራለሁ! ልጅነቴ ውስጥ ምን አይነት ተጽእኖ እንደነበረው አንዳንድ ቃላትን ከፊልም ከሰማሁት እየቀላቀልኩ እነግራቸዋለሁ። እንደሚወዱት እርግጠኛ ነበርኩ። ሻሩክ የእነሱም የእኛም ልጅነት ውስጥ አለ! የለቱ ለተ የሮትራክት ኩሪፍቱ አባላት በአሉን ከአንድ የአረጋውያን መርጃ ማዕከል በጋራ ነበር ያከበርነው። ሜትሪና እነሱ በጣም ጠዋት ሳይሆንባቸው፣ እኛም ጋር ጸሐይ ሳትጠልቅ የሚያገናኘን አመቺ ነው ባልችበት ሰዓት ከአንድ ሆቴል ገብተን ተሰናዳን። ሲነበቡ የሚያኮላትፉ ስም ያለቸው ሰዎች የውውይት ሊንኩን Join ማድረግ ጀመሩ። የሞነጫጨርኩበትን ወረቀት አወጣሁ። ራሳችንን አስተዋወቅን። የተዘጋጀሁበትን በድሮን ዘመን ቆመጠብቀኝን የመሠለ እንግሊዝኛ ማቅረብ ተያያዝኩ። አንዳንድ ቃላት በቃ መገለጽ ሚችሉት በአንድ ቋንቋ ብቻ ነው።ከንድ አረፍተ ነገር ጨርሼ ቆም እላለሁ። ይጠብቁኛል። ስለ ሻሩክ በተመስጦ አወራሁ እናንተ ህንዶች በBollywood ብዙ ነገር ነግራችሁናል አልኩ።የ bollywoodን አለማቀፋዊነት አደነኩ። ስለ ቡሄ ተረኩ። በአሉን ስናከብር የሚያሳዩ ቪዲዎች አጋራናቸው። ተገላገልኩ! ተራቸው ደረሰ ያቀረብነውን ባህል ወደውታል። ስለ ላሊበላና እና እና አክሱም ያወራነው የእነሱን የ Architecture ስልጣኔ እንዲያወሩን ገፋፍቷቸዋል። ግን አንድ ነገር ደስ አላላቸውም። ግዙፉን የህንድ ፊልም industry በ Bollywood ብቻ ነው የጠቀለልከው አሉኝ። Bollywood ሙምባይ ላይ የተመሠረተ የተወሰነ ህንድ ክፍልን ባህል የሚያሳይ እንጁ የሙሉ ህንድ ገጽታ መገለጫ እንዳልሆነ ነገሩኝ። በ Hyderabed እና Kolkata የሚገኘውን Tollywood የChannaiን Kollywood ረስተሃል አሉኝ። እንዳጋጣሚ ታዳሚዎቻችን ከChennai ነበሩ። የምር በጣም ነበር የደነገጥኩት። ማጥናት ነበረብኝ። ስለ ፊልም industryያቸው በወፍ በረር ከማውቀው በተጨማሪ ማንበብ ነበረብኝ። የዲፕሎማሲ አንዱ ምሰሶ የራስን ብቻ ሳይሆን የሌላን ሀገር ባህል እና ስነ ልቦና ማወቅ ነው። የምንለውን የሚረዱበትን አውድ መገንዘብ። የነገሩን መረጃ በጣም እንዳስደመመኝ እና ስለ ፊልም Industryያቸው አድማስ በደንብ እንደማጠና ቃል ገባሁላቸው እና ተለያየን። ያ ቀን ትልቅ ትምህርት የወሰድኩበት ነው! ከመጻፍም ሆነ ከማውራቴ በፊት በቂ መረጃ እንዳለኝ እንድፈትሽ አድርገጎኛል። Rotaract አይደል ክለቤ! ከስህተቴ ከተማርኩባቸው በርካታ አጋጣሚዎች አንዱ ሆኖ አልፏል። ይህን ሁሉ የጻፍኩት እንግዲህ እኔ ወንድማችሁ ቡሄን በእንግሊዘኛ ለህንዳውያን ያቀረብኩ ሰው ብዬ ለመጎረረር ነው😂 ቸር ያቆየን!

76 views
12•••89101112•••1415