የቅርብ ጊዜ ልጥፎች
ገጽ 11 ከ 15 · 169 ልጥፎች
ታትሟል ኤፕሪ 24
ታትሟል ኤፕሪ 18
የአፍላቶክሲን ነገር! ጊዜው 2008ዓ.ም ነው። የዓለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት (ILRI) በአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ባሉ አከባቢዎች የወተት ናሙና በመውሰድ ባደረኩት ጥናት በአውሮፓ ከተቀመጠው ልክ በላይ 'የአፍላቶክሲን' መጠን አግኝቻለሁ ሲል አሳወቀ። ILRI በወቅቱ ለ40 አመታት ያክል በኢትዮጵያ እንስሳት ሀብት ላይ ምርምር ሲያደርግ የቆየ ተቋም እንደመሆኑ ጥናቱ ትልቅ ትኩረት አግኝቶ ነበር። ሰዎች በተሰራጨው ዘገባ ምክንያት የመጠጣት ፍላጎታቸው በፍርሃት ቀንሶ ወተት የሚጠጣ ሰው ሲያገኙ " ወተት አሁንም ይጠጣል እንዴ?" እያሉ ለመጠየቅ ዳርጓቸው ነበር። አስተናጋጆች ቤታቹ ምን አለ ሲባሉ የወተት ዘር መጥራት ፈርተው ነበር ፣ የወተት አምራች ኩባንያዎች በብዙ ሺ ጋሎን የሚሰፈር ወተት ደፍተው ለኪሳራም ተዳርገዋል። በወቅቱ የእንስሳት እና ዓሳ ሀብት ልማት ሚኒስቴር እና በILRI አማካኝነት በጥናቱ አዘጋገብ የተነሳ በርግጎ የነበረው የወተት ገባያ ለማረጋጋት የተለያዩ መግለጫዎች ይወጡም ነበር። የዛኔ 'አፍላቶክሲን' በኢትዮጵያ ከህፃን እስከ አዋቂ የሚያውቀውና የሚጠራው ታዋቂ ስም ሆነ። ይህ በእንስሳት ሀብትና ንግዱ ዘርፍ አወዛጋቢ ከሚባል ታሪኮች አንዱ ነው። የሆነው ሆነና አፍላቶክሲን ምንድነው? አፍላቶክሲን "አስፐርጊለት ፍሌቨስ" ፣ "አስፐርጊለስ ፓራስቲከስ" በሚባሉ የፋንገስ ዝርያዎች እና መሰሎቻቸው አማካኝነት በሚፈጠር ሻጋታ ውስጥ የሚገኝ መርዛማ ኬሚካል ነው። ሻጋታ የሚፈጠረው ምርት እርጥበቱ ሳይጠፋ በሚከማችበት ጊዜ አልያም ኬሚካሉን አመንጪ የሆኑት ፋንገሶች "ስፖር" እህሎች በሚዘሩበት እርሻ ውስጥ ተሰራጭቶ ሲገኝ ነው። ሞቃታማና እርጥበት አዘል በሆኑ የዓለም አከባቢዎች በተለይ ከሰሃራ በታች በሚገኙ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገሮች ውስጥ በሚመረቱ እህል ዓይነቶች ውስጥ አፍላቶክሲን በብዛት ይገኛል። ቅርፊት ያላቸው እንደ በቆሎና ለውዝ ያሉ የእህል ዘሮች በእርጥበታማ ቦታዎች በሚከማቹበት ጊዜ በቅርፊታቸው እርጥበት የመያዝ ባህሪ ስላላቸው የመሻገት ዕድላቸው የሰፋ ነው። ለውዝ፣ በቆሎ፣ የጥጥ ፍሬ ፣ ቦሎቄ ፣ በርበሬ ፣ የተለያዩ ቅመማ ቅመሞች ወዘተ በምርት ክምችት ወቅት በሚፈጠር ስህተት ምክንያት አፍላቶክሲን በከፍተኛ መጠን ሊገኝባቸው ይችላል። በተጨማሪም የእንስሳት መኖዎች በእርጥበታማ አከባቢ ሲከማቹ እና ሳይሌጅ በሚዘጋጅበት ወቅት ነፋስ እና እርጥበት በሚያገኝበት ሁኔታ ከተቀመጠ በቀላሉ ሻጋታ ሊሰራ እና አፍላቶክሲን በመኖ ውስጥ ሊገኝ ይችላል። የአለም የእህል ምርት 25% በአፍላቶክሲን ይበከላል። አፍሪካም ባላት አየር ጠባይ ሳብያ 80% የሚሆኑ ሕዝቦቿ ለአፍላቶክሲን ጉዳት የተጋለጡ መሆናቸውን ጥናቶች ያመለክታሉ። በአንድ ሀገር ውስጥ በእንስሳት መኖዎች እና በሰዎች በተለይ በህፃናት ምግብ ውስጥ የሚገኘው አፍላቶክሲን ቁጥጥር የማይደረግበት ከሆነ እና የምርት አከመቻቸት ዘዴው አፍላቶክሲንን ያላማከለ ከሆነ በዋናነት ሁለት መሠረታዊ ችግሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉ። የጤና መታወክ እና የኤክስፖርት ንግድ መቀነስ! አፍላቶክሲን ወደ ሰውነት እንደገባ "ሜታቦላይዝ" የሚደረገው በጉበት ነው። ለብዙ ጊዜ በከፍተኛ መጠን ለዚህ ኬሚካል ጉበት ተጋላጭ ሲሆን የጉበት ካንሰር ሊያስከትል ይችላል። B1 ፣ B2 ፣ G1 ፣ G2 የሚባሉ ሰብሎች ላይ የሚገኙ እና M1፣ M2 የሚባሉ እንስሳት እጽዋቶቹን ከተመገቡ በኋላ "ሜታቦላይዝ" በማድረግ የሚፈጥሯቸው የአፍላቶክሲን አይነቶች አሉ። B1 የጨጓረሠ ካንሰር ሊያስከትል የሚችል ነው። M1 የሚባለውም መጠኑ በእንስሳት ተዋጽኦ ውስጥ እጅግ ከፍ ሲል መርዛማ ነው። በተጨማሪም አፍላቶክሲን የሰውነት በሽታን የመከላከል አቅምን ይቀንሳል። በህፃናት ላይ የእድገት ውስንነት፣ የጉበት በሽታ፣ ከፍተኛ የሆነ የበሽታ ተጋላጭነት እና ለካንሰር የመጠቃት እድል ከፍተኛ መሆን ሊያስከትል ይችላል። አፍላቶክሲን በከፍተኛ መጠን በመኖዋቸው ውስጥ የሚገኝ እንስሳትም የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ ምርት እና እድገት ማሽቆልቆል፣ በበሽታ ቶሎ ቶሎ የመጠቃት ነገር ሊስተዋልባቸው ይችላል። እንደ ወተት ባለ ተዋጽዋቸው ውስጥም ኬሚካሉ ይኖራል። ይህንን መጠነ ሰፊ የጤና ጉዳት ለመከላከል ታድያ የተለያዩ ሀገራት በተለይ ያደጉ የምንላቸው በምግብ ምርት ውስጥ መገኘት ያለበትን የአፍላቶክሲን መጠን ወስነዋል። በርግጥ አፍላቶክሲን በውስጡ የሌለ ምግብ ማለት የሚቻል ባይሆንም አውሮፓ ከ0.05ug/kg በላይ የሆነ አፍላቶክሲን ያለበት ምግብ መርዛማ ነው ትላለች። አሜሪካም ከ0.5ug/kg በላይ የሆነ አፍላቶክሲን የሚገኝበት ምግብ በገበታ ላይ እንዲኖር አትፈቅድም። ለዚህም ጥብቅ የሆነ ቁጥጥር ወደ ሀገራቸው በሚገቡ ምግቦች ላይ ያደርጋሉ። ሀገራት ይህን መስፈርት የሚያወጡበት የተለያዩ መንገዶች ይኖሯቸውዋል። ሀገራችንም ካለችበት ደረጃ ጋር በማመዛዘን ከ2008ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ኤጄንሲ አማካኝነት ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የምግብ ውጤቶች ልኬት የምታደርግ ሲሆን ከ5ug/kg በላይ የB1 አፍላቶክሲን የሚገኝበት ምርት ጥቅም ላይ እንዲውል አይፈቀድም። ለህፃናት ምግብ ደግሞ መጠኑ እስከ 2ug/kg ዝቅ ይላል። ከላይ ከዘረዘርኳቸው ነገሮች እንደምንረዳው አንድ ሀገር ወደ ሌላኛው ሀገር የምግብ ውጤቶችን ኤክስፖርት ማድረግ ሲፈልግ የተቀባዩን ሀገር የአፍላቶክሲን ገደብ ማወቅና ማክበር አለበት። ለዚህም በቂ ቁጥጥር እና ህግ በማይኖር ከሆነ የኤክስፖርት ንግዱ እለት እለት ማሽቆልቆሉ የማይቀር ነው። የቅርብ የሆነ መረጃ ባይኖረኝም በተለይ ወደ እንግሊዝ ሀገር በኮንቴነር ሳይቀር የተላኩ በሺ ቶን የሚለኩ ቅመማ ቅመሞች በዚሁ አፍላቶክሲን ጣጣ ወደ ኋላ ተቋጥረው እኖዲመለሱ ተደርገዋል። መገኘት የነበረበትም የውጪ ምንዛሪ ወሃ በልቶታል። እንደ ኢትዮጵያ ላለች የውጪ ምንዛሪዋ በግብርና ውጤቶች ላይ ለተንተራሰ ሀገር ይሄ ቀልድ አይደለም። ይልቅ አንድ ሌላ አንድ ቀልድ አውቃለሁ፤ ሰውዬው ርቦት ቤቱ ገባ፣ የጓዳውን ፋኖስ አብርቶ ቢያይ ከመሶቡ ከአንዲት ስትበላ የተረፈች ሻጋታ ዳቦ በቀር አንዳች አልነበረም። ሰውዬው የሆዱን ጥያቄ አልቻለም እና የሻገተ በላህ የሚለውን የአእምሮ ጥያቄ ለመሸሽ ሲል ዳቦዋን ፋኖሱን አጥፍቶ በላት። አፍላቶክሲን የዋዛ አይደለም ለሚነገሩን ሳይንሳዊ እውነቶች መብራታችንን እያጠፋን ደጋግመን ብንበላው ነገ በሽታ ሆኖ ይመጣል። ጉዳዩ ብዙ የሚባልበት ቢሆንም እኔ እዚህ ጋር ላብቃ። በቀጣይ ከቻልኩ ሻጋታ የሚፈጠርበትን ባህላዊ የምግብ አከማቸታንን ለመዳሰስ እሞክራለሁ። ከላይ ያለውን ሀሳብ ያጠናከርኩላችሁ የተለያዩ ጥናቶችን በማንበብ እና በተለይ ሮይተርስ በተለያዩ ጊዜያት ስለ አፍላቶክሲን ያወጣቸውን መረጃዎች በመዳሰስ ነው። በዘርፉ ጥናት ያደረጋችሁ ሰዎች ደግሞ ወቅታዊ የአፍላቶክሲን መረጃዎችን ጀባ ብትሉን ደስታዬ ነው። ለታጋሽ ንባባችሁ አመስጋኝ ነኝ! ቸር ያቆየን!!
ታትሟል ኤፕሪ 18
ታትሟል ኤፕሪ 17
የማስታወቅያ ሐይል! I took a wonderful lesson from Professor Alemayehu Today. በአአዩ በሚገኘው ኮሌጃችን በየ 15 ቀኑ በተለያዩ በሞያቸው ትልቅ ልምድ ባላቸው መምህራኖቻችን እና ተመራማሪዎች ሴሚናሮች ይቀርባሉ። እስካሁን መገኘት የቻልኩባቸውን ሁሉ የተሳተፍኩ ሲሆን በተለይ በእንስሳት ፣ በጤና እና ተዛማች ጉዳዮች ከሀገር ውስጥ እንዲሁም ከውጪ በመጡ ምሁራን በቀረቡ የጥናት ጭምቀ ሀሳቦች ብዙ ነገር ተገንዝብያለሁ። ክፍል ውስጥ ከምማረው በላይ በሚያነቃቃ እና ለመመርመር በሚያጓጓ መልኩ የቀረቡ ናቸው ብል ማጋነን አይሆንም። በተጨማሪም በቀረቡት ጽሑፎች ላይ የሚሰጡ አስተያየቶች የሚነሱ ጥያቄዎች እና ክርክሮ ደስ የሚል ጣዕም ያላቸው እና የእኔንም የማወቅ ፍላጎት ያሳደጉ ናቸው። እንዲህ ያሉ ሞያዊ ውይይቶች እና ክርክሮች ደስ ይላሉ! ወደ ዋና ጉዳዬ ስመጣ ዛሬ በፕሮፌሰር አለማየሁ የቀረበው ሴማናር መነጋገርያ የሆነው ገና ማስታወቅያው ከተለጠፈበት ጊዜ ጀምሮ ነበር። "Weird Science" ይላል። Everyone was wondering which part of science is weird. ሰአቱ እየቀረበ ሲመጣ ሰዎች ከፕሮፌሰሩ የእውቀት አድማስ በመነሳት የተለያዩ ግምቶቻቸውን ሲሰነዝሩ ነበር። እኔ እና የድህረ ምረቃ ትምህርቷን በማይክሮ ባዮሎጂ እያጠናች ያለች ወዳጄም ግምታችንሰ ስንከራከርበት ነበር። She said " Microbiology is the weird science" ለራስ ሲቆርሱ ተባብለን ተቀላልደናል። ፕሮፌሸር ገና አዳራሽ ውስጥ ሳንገባ ቀልባችንን ወስደውት ነበር። ዋና ሊነግሩን የፈለጉትን ሀሳብ ሸሸግ አድርገው ብዙ እንድንወያይ ብዙ እንድንጠብቅ አድርገውናል። የማስታወቅያ ሀይል ይህ ነው። -የተደረሳሲን የትኩረት አቅጣጫ ማወቅ። -አእምሮ ውስጥ ጥያቄ መፍጠር። -የጠየቁትን ትያቄ መልስ ማግኛ ቦታው መርሃ ግብሩ ብቻ እንደሆነ እንዲያስብ ማድረግ። Don't judge a book by its cover ቢባልም የሚስብ እና ጥያቄ የሚፈጥር ልባድ ያለው መጽሐፍ ግን ቶሎ የመሸጥ እድል አለው። ፕሮፌሰር ሀሳቡን ምን እንደሆነ ሳናውቅ ነው የሸጡልን። እንደገመትኩት አዳራሹ በሰው ተሞልቶ ነበር። ብዙ ሴሚናር የማይገኙ አዳዲስ ፊቶችም አይቻለሁ። ልክ የሴምናሩ ሙሉ ርዕስ በማቅረብያ ስክሪኑ ሲከፈት በፕሮፌሰር አለማየሁ ለማ weird የተባለውን ሳይንስ አወቅን። የአጥቢ እንስሳት ስነ ተዋልዶ ጉዳይ ነው። እርሳቸው ደግሞ በዚህ ዘርፍ ከሀገር ተርፈው ለአለም ብዙ ያስተማሩ ናቸውና የሚነግሩንን ለመስማት ጆሯችንን አቆምን። የሚናገሩትን ያውቃሉና አላሳፈሩንም። እጅ በአፍ አስይዞ የሚያስቅ የሳይንስ ጉድ ሰምተን ተወያይተንበት ወጣን። ዋናው ልነግርህ የፈለኩት ነጥብ በእጅህ ያለውን ሀሳብ እንዴት አንድርገህ እንደምታስተዋውቀው አስበህበታል ወይ ነው! የያስከው ሀሳብ ምንም ጥኡም ቢሆን ሳቢ በሆነ መንገድ አዘጋጅተህ ጥሱ ማስታወቅያ ሰርተህ ሰሚ ጆሮ ካላዘጋጀህለት መና ይቀራል። ሁሌም ስለ ራስህ፣ ስለ መረጃህ፣ ስለ ምታውቀው ነገር እና ስለ ጥቅሙ የምታስተዋውቅበትን መንድ በሚገባ አስብበት። "Don't judge a book by its cover, but when you're writing a book, it should have a cover that can be judged!" ቸር ያቆየን
ታትሟል ኤፕሪ 17
ታትሟል ኤፕሪ 9
ዶሮ መስጠት አንዳንዴ Malnutrition እንደመስጠት ነውና! As a vet student one of the thing Im Concerned about is the fine details we learn when we are in a production class, the housing system, the angle of the sun, the distance of living house office and latrine from a…
ታትሟል ኤፕሪ 9
ዶሮ መስጠት አንዳንዴ Malnutrition እንደመስጠት ነውና! As a vet student one of the thing Im Concerned about is the fine details we learn when we are in a production class, the housing system, the angle of the sun, the distance of living house office and latrine from a farm, equipment we must have , their structure and correct installation, the safety protocol details etc...if you take poultry class we even learned what the color of drinking equipment should be! At the early time I were saying :" why so serous about equipments? TThis is just westing time instead of learning the bulk medicine part! Now! I found the reason and I really loved the way we give impasses for everything in a production. The principle even helped in my day to day life. if I want to now the reason why something is not happening as my expectation I focus on the details, I will focus on why and why not. Details have a magic! If you know the reason why your Chickens stressed you can have the clue of solving it, I don't expend a lot of money on it, you will not use a lot of drugs and expose the pathogens for drugs to lead them have a resistance on it, you will just the light intensity of your lamp and everything gonna be ok in a few days. ከላይ የተጠቀምኩትን ርዕስ የወሰድኩት የ 35ተኛው የኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ማህበር አመታዊ ጉባኤ ላይ ከቀረቡ ጥናታዊ ጽሑፎች መካከል ዶ/ር አንተነህ ኡመር " Effect of a child-owned poultry intervention providing Eggs on nutrition status and motor skill of young children in southern Ethiopia : A cluster randomized and controlled Community Trial." በሚል ርዕስ ሲያቀርብ ከተናገረው በመቀንጨብ ነው። ዶ/ር አንተነህ እንደ እኔ በአያት እጅ ያደገ ነው። በልጅነቱ ዶሮዎች ነበሩት። የሚወልዱት እንቁላል የሱ ነው፤ የመንከባከብ ሐላፊነቱም እንዲሁ። አንተነህ በልጅነት እድሜው ሀላፊነት እና ሀላፊነቱ የሚሰጠው በረከት ነበረው። ዶሮ ሲሞት ዶሮ እየተተካ የራሱን ሰውነት እና ብሩህ አእምሮ የሚገነባበት ፕሮቲንን ራሱ ከተንከባከባቸው ዶሮዎች እያገኘ አድጓል። አድጎ ለቁምነገር ሲበቃ እና የመፍትሔ ሰው መሆኛው ሲደርስ የአያቱ ስልት ገባው። በጥናት ሊፈትሸው ወደደ። ለእኛ ሲነግረን "የዚህ ጥናት ባለቤት እኔ ሳልሆን አያቴ ነች" ብሎናል። ያደገበትን ብልሃት በጥናት ሊያረጋግጥ ወደ ሀላባ እና አከባቢዋ ወረደ። (ጥናቱን ከስር Comment ላይ አስቀምጫለሁ አንብቡት!) ለታዳጊ ህፃናቱ ቤተሰቦቻቸውን በሐይማኖት አባቶች የልጆቻቸውን ዶሮ እንዳይነኩ እያስማለ ሀገር በቀል ዶሮዎችን ሰጣቸው። ትንሹ አንተነህን አደረጋቸው። የኔን ትኩረት የሳበው ይህ አይደለም! እነ አንተነህ ለታዳጊ ህፃናቱ እየተንከባከባችሁ አሳድጉና እንቁላላቸውን ተመገቡ ብለው ዶሮ ሲሰጣቸው አብረው የዶሮ ቤትም አድለዋል። ለምን? "አንዳንዴ ዶሮ መስጠት Malnutrition እንደመስጠት ይሆናልና!" ህፃናቱና ዶሮዎቹ ጥምብቅ ግንኙነት መኖራቸው አይቀሬ ነው። ዶሮዎቹን ቤት ሊያሳድሯቸው ይችላሉ... ይህኔ ኩሳቸው በትክክል ካልተወገደ እንደ Campylobacter ላሉ በሽታ አምጪ ተዋስያን ጥሩ በራብያ አገኙ ማለት ነው። Cambylobacter ከ5-14% ለሚሆነው የህፃናት ተቅማት መንስኤ ነው።ከሳምንት በላይ እድሜ ያላቸው ዶሮዎች ደግሞ ምንም ምልክት በላያቸው ላይ ሳያሳዩ በሽታውን ያዛምታሉ። ተቅማት በበረታ ቁጥር ህፃናቱ ከዶሮዎቹ ከእንቁላል ይልቅ በሽታ ሸመቱ ማለት ነው። ጥሩ ነፍስ የሚያገኝ፣ ቅንብብ ተደርጎ የተሰራ የዶሮዎች ቤት ግን ለባክቴርያው ምቹ ቦታን ይነፍገዋል። ስለዚህ ከላይ ያነሳነው ስጋት አይኖርም! ይህ ነው የስራን እያንዳንዱን details የማወቅ ጥቅም! ጥናቱን እየተከታተልኩ ትኩረቴ ከተማርኩት ነገር ጋር አብሮ ብን ብሎ ነበር። ዋናው ጥያቄ በተለይ የእንስሳት እርባታ ላይ የተሰማራችሁ ሰዎች ችግሮችን ቀድሞ ለመከላከልም ሆነ ከተከሰቱ በኋለሠ ለማስወገድ ስለ እንስሳቶቻችሁ ፣ ስለ ቤታቸው ፣ ስለ አያያዛቸው እና ስለ እያንዳንዱ Farm ውስጥ ያለ ነገር ምን ያክል ታጤናላችሁ ነው? ላስተዋለ ልብ ላለ ላወቀው፣ መፍትሄ ከእጅ ነው! ቸር ያቆየን!
ታትሟል ኤፕሪ 9
ታትሟል ኤፕሪ 7
ስለ ነጭ ወርቅ ላወራችሁ ነው! ወርቅ የሀብት፣ የጥሪት መገለጫ ነው። እኔ የማወራችሁ ነገር ነጭ ወርቅ ያሰኘው ግብሩ ነው። በበረሃ መኖርን የሚቻል ያደረገ በኢትዮጵያ ከቆላማው ሀረርጌ ጀምሮ እስከ አለማችን ዝቅተኛው ስፍራ የአፋር ስምጥ ሸለቆ ድረስ ተወዳጅ የሆነ፣በጠንካሮቹ፣ ጥርሰ ነጫጮቹ፣ ሀገር ወዳዶቹ ባለ ሽርጦች፣ የዘመናት ባህል ባለቤቶች እና የሰው ዘር መገኛን ስፍራን ሐሩር ክብደት ለአኗኗራቸው አሰግደው በሚኖሩት የአፋር ፣ የኢትዮጵያ ሶማሌ ፣ ቦረናና ከረዩ ህዝቦች በፍቅር የሚጠጣ። የበረሃው መርከብ ከተባለው የጽናት ምሳሌ፣ ከግመል የሚገኝ! አዎን የማወራው ስለ ግመል ወተት ነው። ስለ በረሃው ነጭ ወርቅ! የግመል ወተት ነጣ ያለ በሠጠኑ ክሬም የሚመስል ቀለም ያለው ወተት ነው። ቀለሙ ከላም ወተት ጋር ብዙም የሚራራቅ አይደለም። ጣዕሙ ወተቱን የምትሰጠው ግመል ለመብላት እንደምታዘወትረው እፅዋት ቢለያይም ጨው ጨው የማለት ባህሪ አለው። ለመጀመርያ ጊዜ ለሚቀምሰው ሰው ከበድ ሊል የሚችል የተለየ ሽታም ይኖረዋል።ብዙዎቻችን የላም ወተትን በአንድም በሌላ በደንብ እናውቃለን። ይህኛው ከዛ ቀጠን ይላል። እያደር ይኮመጥጣል እንጂ አይረጋም። ወተት ሲረጋ ቅቤ ይወጣዋል ብሎ ነገር በግመል ወተት ፉርሽ ነው። ከግመል ወተት ቅቤ ማውጣት የዋዛ አይደለም። በውስጡ የያዛቸው ንጥረ ነገሮች ወሃ ከ86-88%፣ Fat(ቅቤ) 2.9-5.4% ፣ ፕሮቲን 3.0-3.9% ፣ ስኳር(Lactose) 3.3-5.8% የተለያዩ ጠቃሚ ቫይታሚኖች እና ሚነራሎች ናቸው። በግመል ወተት ውስጥ ያለው የቅቤ መጠንን ስንመለከት አነስተኛ የሚባል አይነት ነው። በተጨማሪም ከላም ወተት ቅቤ አንጻር ስንመለከት የቅቤ ቅንጣቶቹ (Fat globules ) እጅግ ትንሽ (Size) ነው ያላቸው ይህም ለምግብ መፈጨት ስርዓቱ ቀለል ያለ እና የተመቸ ወተት ያደርገዋል። አንዳንድ ወተት የሚጣላቸው ሰዎች አሉ። Lactose intolerance! በወተት ውስጥ የሚገኘው የስኳር አይነት lactose ይሰኛል። አንዳንድ ሰዎች ሰውነታቸው lactoseን እንዲፈጭ የሚያግዝ Enzyme በበቂ ስለማያመርት ወተት በሚጠጡ ወቅት አይስማማቸውም። ጉደኛው የግመል ወተት ግን ለነዚህ ሰዎች ይመከራል። ምክንያቱም የLactose መጠኑ እጅግ አነስተኛ ነው። የግመል ወተት አጓት (whey) በውስጡ ለጤና እጅግ ጠቃሚ የሆኑ እና በሽታ ተከላካይ ፕሮቲኖችን ይዞ ይገኛል። ቅጠል ተመጋቢዋ ግመል ከ1000 በላይ የተለያዩ አይነት ቅጠላቅጠሎችን በመቅጠፏ ምክንያት ወተቷ መድሀኒት አያጣውም። ለቁስል መሻያ፣ ለስኳር በሽታ ፣ ኦቲዝም እና አልዛይመር የግመል ወተት የሚበጀው ነገር አለ የሚሉ ትናቶችን ተመልክቻለሁ። በሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያዊ የሚገኙት የአፋር ህዝቦች ግመል ሀብታቸው፣ መተዳደርያቸው እና የክብር መገለጫቸው ከሆኑ ህዝቦች መካከል ይገኛሉ። ከህይወታቸው ጋር የተሳሰሩ በመሆናቸው ግመሎቻቸውን የሚያደንቁበት፣ የሚያወድሱበት እና ስሜታቸውን የሚገልጹበት ስነ ቃል አላቸው። 'ጋሊሳሬ' ይሉታል ከብዙ መወድሶቹ መካከል ‘‘Carribar qibinah koo naxiggile Kaxxabar buxalih koonaxiggile Macakah abah mawacarriya Urrutabbixi caxah bahta meqrele’’ እንግዳ ቢመጣ በአንቺ ይስተናገዳል አባወራ እራቱን ከጡትሽ ያገኛል አንቺ እስካለሽ ድረስ በጥጋብ ይኖራል የሰው ሀብት አንቺ ነሽ ሁሉም ይመኝሻል፡፡ ግመል ጥበቃ ርቀው የተሰማሩ ወጣት ወንዶች ግመል ሳይጠጣ በፊት ውሃ አይጠጡም፡፡ ሁለት ሶስት ቀን ውሃ ተገኝቶ ባይጠጣና ቢጠሙ ወተቱን አልበው ይጠጣሉ እንጂ ውሃ ከግመሉ ቀድመው አይጠጡም፡፡ ይህም በብርታት ተፈትኖ የፅናት ባህሪውን የመውረስም ምልክት ነው። ይህ ምን ያክል በግመሎቻቸው እንደሚኮሩ አመልካች ነው። ብዙ ነገሮቻች በእጅ ያለ ወርቅ የሆኑብን አይደለን? የበረሃው ነጭ ወርቅ የግመል ወተትም በኢትዮጵያ ሀብቱ ትልቅ ቢሆንም እንደሚገባው ተጠቅመንበታል ብዬ ግን አላምንም።ለዚህ ምክንያቶቹ ብዙ ናቸው። እኛም ስለ ግመል ሀብታችን ጠቅለል ያለ መሠናዶ እያዘጋጀን ነው። ስለ ግመል ተፈጥሮ ፣ ስላለው ፋይዳ፣ ስለ ወተቱ እና እንዴት ለሀገር የሚበጅ ማድረግ እንደምንችል እንዳስሳለን። በቀጣይ ሳምንት https://t.me/campus_voice_2016 ይዚህ ይጠብቁን። ቸር ያቆየን!
ታትሟል ኤፕሪ 7
ለጋሽ ክንዶች ለሁለተኛ ጊዜ ሊዘረጉ ነው! የክለባችን ሁለተኛ ደም ልገሳ ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ? ከታች ባለው ሊንክ ይመስገቡ: https://forms.office.com/Pages/ResponsePage.aspx?id=DQSIkWdsW0yxEjajBLZtrQAAAAAAAAAAAAN__leILWZUMlVBVk5UNlEwOTZJNkFXQTJCNU5FTlBKWS4u For more info: @yared2774 0924751894 Rotaract Family #Rotaract_Kuriftu #Rotary #Rotaract #District9212 #RotaractEthiopia Follow Us: Facebook | Twitter | Instagram | Telegram | LinkedIn
#HaSab #Animal_welfare #Against_Donkey_slaughtering_For_Ejiao የአፍሪካ መሪዎች ጎሽ የሚያስብል ውሳኔ አስተላልፈዋል! ተፈጻሚነቱ የእኛን ክትትል ይፈልጋል። ከዚህ በፊት ይህ ጉዳይ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ Viral ሆኖ ሲዘዋወር ሁላችንም እናስታውሳለን። የአህያ ቄራ ጉዳይ። "At first our governments saw this as an opportunity, and many legal slaughterhouses opened in Africa, But between 2016 and 2019, about half of our donkeys were killed for the trade." ይህን የተናገሩት ዶ/ር ሰለሞን ኦንያንጎ(Dr Solomon Onyango) ከኬኒያው Donkey Sanctuary ከBBC ጋር ባደረጉት ቆይታ ነው። አብዛኛዎቹ ሀገራት ቻይና የአህያ ቆዳ እንድትልኩልኝ እፈልጋለሁ ስትል ጉዳዩን የቆጠሩት እንደትልቅ እድል እና የውጪ ምንዛሪ ማግኛ መንገድ ነበር። ነገር ግን ለኢጃኦ የሚፈለገው የአህያ እርድ ከጥቅሙ ጉዳት የጎላ ሆኖ ተገኝቷል። ያሳለፍነው እሁድ የካቲት 10 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ የመሪዎች ስብሰባ የአለም የአህያ ብዛት 2/3 የሚይዙት 55 ሀገራት ግሽ የሚያስብል ውሳኔን አስተላልፈዋል። በአፍሪካ ለቆዳ ንግድ አህያ ማረድ ከእንግዲህ ወንጀል ይሆናል። ይህ ውሳኔ ተፈጻሚ እንዲሆን ግን የእንስሳት ጤና እና ደህንነት ላይ የሚሰሩ ተቋማትን ብርቱ ክትትል ይፈልጋል። በተለይ በኢትዮጵያ ጉዳዩ የመንግስትን ይሁንታ ያገኘ እና ለህዝብ በቂ የሆነ መረጃ የሚሰጥበት ግልጽ ንግድ ባለመሆኑ በርግጥም ይህ ውሳኔ ተፈጻሚ መሆን አለመሆኑን እየተከታተለ ለህዝብ የሚያደርስ እና የሚጠይቅ አካል መኖር ግድ ይለዋል። ለዚህ ተቀዳሚዎቹ ባለ ሀላፊነቶች እኛው በዘርፉ ያለን ባለሞያዎች ነን። ሁሉም ሰው እንዲገነዘብ የምፈልገው ነገር ቢኖር ይህንን ንግድ የምንቃወምበት አበይት ምክንያት ንግዱ ቀጣይነት የሌለው እና ከጥቅሙ ጉዳቱ የሚያመዝን በመሆኑ ነው። ይህን ቻይና ራሷ ተመልክታዋለች። ከዚህ ቀደም የኢጃኦ ፍላጎቷን ለማሟላት ከራሷ ብቻ የአህያ ቆዳ ትጠቀም የነበረ ቢሆንም በሀገሪቱ የሚገኘው የአህያ ቁጥር እጅግ በመመናመኑ ፊቷን ወደሌሎች ሀገራት አዙራለች። ፊቷ የዞረባቸው ሀገራት ሁሉ በዚህ ንግድ መጎዳታቸውን አምነዋል። በአጠቃላይ የቻይና የአህያ ቆዳ ፍላጎት አለም ካላት 53 ሚልየን አህያ ቁጥር ጋር አይመጣጠነም። በአፍሪካ ለአህያ ደህንነት መሟገት ቅንጦት አይደለም! ለገጠር ማህበረሰብን ህልውና መቆርቆር እንጂ። ቸር ያቆየን! ያሬድ ኤርሚያስ